“በሰላማዊ ትብብር አስተማማኝ የባሕር መዳረሻን ማረጋገጥ ለኢኮኖሚያዊ የወደፊታችን እና በአፍሪካ ቀንድ የረዥም ጊዜ መረጋጋት እና ብልጽግና እንዲኖር አስፈላጊ ነው” 

Date:

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ትስስር እና የባሕር ተደራሽነት ለኢትዮጵያ ዘላቂ ልማት ያለው ጠቀሜታ ወሳኝ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ በአቪዬሽንና በዲጂታል መሠረተ ልማት ዘርፍ ከፍተኛ ስራን እየሰራች መሆኑን ገልጸዋል ፡፡

“በኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰዎችን እናገናኛለን፣ ገበያዎችን እናስተሳስራለን እንዲሁም ሸቀጦችን እናንቀሳቅሳለን፤ ይህንንም ፍጥነት ለማስቀጠልም አኅጉራችንን በዓለም አቀፍ የእሴት ሰንሰለት ማዕከል የሚያደርጋትን የቀጣይ ትውልድ መግቢያ በር የሆነ በአፍሪካ ትልቁን አየር ማረፊያ እየገነባን ነው” ብለዋል።

ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ላላት ኢትዮጵያ የረዥም ጊዜ ብልጽግና የተለያዩ የመዳረሻ መንገዶችን እንደሚፈልግ አፅንኦት ሰጥተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮ ቴሌኮም በመላው አፍሪካ መስፋፋት ዲጂታል መከፋፈል አሻጋሪ ድልድይ ለመሆን እና አኅጉራዊ ውህደትን ለማጠናከር የሚደረገው ጥረት አንዱ አካል መሆኑን አንስተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...