በሰሜን አሜሪካ የሚካሄደው “ግራንድ አፍሪካን ራን” ከአጋሮቹ ጋር ተፈራረመ

Date:

ጊፍት ሪልስቴት እና አሪፍ ፔይ ከኖቫ ኮኔክሽንስ ኩባንያ ጋር ታላቁን የአፍሪካ ሩጫ እንደዚሁም የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድን በቀጣይ ዓመታት በአብሮነት ለማዘጋጀት ሰኔ 27/2017 ዓ.ም በአዲስአበባ በስካይላይት ሆቴል ስምምነት ፈፀሙ። ላለፉት ዓመታት በአጋርነት የቆየው አርትስ ቴሌቭዥንም በተመሳሳይ ስምምነት አከናውኗል።

በዕለቱም የግራንድ አፍሪካ ራን የ2025 የሩጫ ውድድር የመሮጫ ቲ-ሸርት በአምራቹ ጎፈሬ አማካይነት ይፋ ኾኗል።

“አብሮነት መሻል ነው” በሚል መሪ ቃል ቀጣዩ ውድድር በአመዛኙ ኢትዮጵያውያንንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ባሳተፈ መልኩ እኤአ ኦክቶበር 11 /2025 በዋሽንግተን ዲሲ የሚከናወን ሲኾን ኦክቶበር 12/2025 ደግሞ በመልካም ተግባራቸው ተፅዕኖ ለፈጠሩ ኢትዮጵያዊያን የዕውቅና መርሐግብር የሚሰጥበት አፍሪካን ኢምፓክት አዋርድ ይከናወናል።

በትላንቱ መርሐግብር ላይ የአፍሪካ ግራንድ ራን ቤተሰቦች፣ ታዋቂ አትሌቶች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የአፍሪካ ግራንድ ራን አጋሮች ዳሸን ባንክ፣ ጎፈሬ ስፖርት፣ አሌክሳንደሪያ ቶዮታ፣ ሮሚንግ ሮስተር፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን እንዲሁም አዳዲሶቹ አጋሮች ጊፍት ሪልስቴት፣ አሪፍ ፔይ በተወካዮቻቸው አማካይነት በአካልና በኢንተርኔት የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን ገልፀዋል።

ዶ/ር ጋሻው አብዛ፤ የግራንድ አፍሪካን ራን መሥራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ባለፉት ዓመታት አብረዋቸው ለተጓዙና ላገዟቸው ቤተሰቦች በሙሉ ላልተቋረጠ አጋርነታቸው ከፍ ያለ ምሥጋና አቅርበዋል።

ድሬቲዩብ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ ጋር ይኖራሉ

በኢትዮጵያ ከ10 ሚልዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ እና ከ2...

የቶዮታ ኮሮላ መኪና በኤሌክትሪክ ሊመጣ ነዉ

የዓለማችን ግዙፍ የመኪና አምራች የሆነው ቶዮታ፤ እንደ ቴስላ እና...

ኢራንን ለመምታት የዩናይትድ ስቴትስ ጄቶች ከምድሯ ይነሱ እንደነበር እሥራኤል ይፋ አደረገች

የእሥራኤል መከላከያ ሚንሥትር እሥራኤል ካትስ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ጄቶች...

በጋምቤላ ክልል በጀት ዓመት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ2 ቢሊዮን በላይ ጭማሪ አሳየ

 በጋምቤላ ክልል በበጀት አመቱ በተከናወነው የገቢ አሰባሰብ ዙሪያ የተሻለ...