በአዲስ አበባ ለጨረታ ለቀረቡ ቦታዎች በካሬ ሜትር 265 ሺሕ ብር መሰጠቱ ታወቀ

Date:


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬትና ልማት አስተዳደር ቢሮ ለጨረታ ካቀረባቸው 427 ቦታዎች ውስጥ፣ የቀረበው ከፍተኛ ዋጋ በካሬ ሜትር 265 ሺሕ ብር መሆኑና ቦታውም ካዛንቺ እንደሆነ ታወቀ፡፡፡
የመሬትና ልማት አስተዳደር ቢሮ የመሬት ዝግጅት ባንክና ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ተስፋዬ እንደገለጹት፣ በአምስተኛ ዙር እየተካሄደ በሚገኘው የመሬት ሊዝ ጨረታ 18 ሔክታር መሬት ቀርቧል፡፡
በሊዝ ለማጫረት ከቀረቡ ቦታዎች ውስጥ ካዛንቺስ የሚገኝ አንድ ቦታን በካሬ ሜትር 265 ሺሕ ብር ለመግዛት ከተጫራች ዋጋ መቅረቡን፣ እስካሁን በአምስት ክፍላተ ከተሞች በተደረገው የጨረታ ሒደት 76 ተጫራቾች በጊዜያዊነት ጨረታውን ማሸነፍ መቻላቸውን አክለው ገልጸዋል፡፡
ለጨረታው የቀረቡ ቦታዎች የሚገኙት በዘጠኝ ክፍላተ ከተሞች እንደሆኑ የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ በአጠቃላይ የጨረታ ሰነዱን ገዝተው የተጫረቱት ብዛት 6,885 ተጫራቾች  እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡
@ሪፖርተር

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...