በአፋር ክልል ባራሕሌ ወረዳ በመሬት መንቀጥቀጥ ጉዳት መድረሱ ተሰምቷል
አፋር ክልል ሰሜናዊ ዞን በባራሕሌ ወረዳ ቅዳሜ ጥቅምት 1 2018 ዓ.ም ምሽት በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሰውና ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል ተብሏል።
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አሊ ሁሴን በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት በቡሬ እና ዓስጉቢ ቀበሌዎች በርካታ ቤቶች መፍረሳቸውን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል።
በአደጋው እድሜው 12 ዓመት የሆነ ልጅ ህይወት ማለፉን ገልጸው÷ 6 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን አስረድተዋል።
ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ በትግራይ እና አፋር ክልሎች የተለያዩ አካባቢዎች የተሰማ ነው።
በመሬት መንቀጥቀጡ 43 ሺህ 4መቶ56 የሚሆኑ ሰዎች ቤቶቻቸው ሙሉ በሙሉ መውደሙን እና ያለመጠለያ መቅረታቸውን ጠቁመዋል።
ለተጎጂዎች ድጋፍ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ዋና አስተዳዳሪው ገልጸዋል።
ጥቅምት 02/2018 ዓ.ም
በአፋር ክልል በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የሰው ህይወት ሲያልፍ ከ43 ሺህ በላይ የሚሆኑ ሰዎች መኖሪያቸው መውደሙ ተገለፀ
በአፋር ክልል ባራሕሌ ወረዳ በመሬት መንቀጥቀጥ ጉዳት መድረሱ ተሰምቷል
አፋር ክልል ሰሜናዊ ዞን በባራሕሌ ወረዳ ትናንት ምሽት በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሰውና ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል ተብሏል።
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አሊ ሁሴን በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት በቡሬ እና ዓስጉቢ ቀበሌዎች በርካታ ቤቶች መፍረሳቸውን ተናግረዋል።
በአደጋው እድሜው 12 ዓመት የሆነ ልጅ ህይወት ማለፉን ገልጸው÷ 6 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን አስረድተዋል።
ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ በትግራይ እና አፋር ክልሎች የተለያዩ አካባቢዎች የተሰማ ነው።
በመሬት መንቀጥቀጡ 43 ሺህ 4መቶ56 የሚሆኑ ሰዎች ቤቶቻቸው ሙሉ በሙሉ መውደሙን እና ያለመጠለያ መቅረታቸውን ጠቁመዋል።
ለተጎጂዎች ድጋፍ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ዋና አስተዳዳሪው ገልጸዋል።
