በኦሮሚያ ክልል የ4.5 ሚሊዮን ዶላር የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ

Date:

ፈያ ኢንተግሬትድ ዴቬሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን በኦሮሚያ ክልል የሚከሰቱ የበሽታ ወረርሽኞችን እና አጣዳፊ የምግብ እጥረት ችግሮችን ለመከላከል የሚያስችል የ4.5 ሚሊዮን ዶላር ፕሮጀክት በይፋ መጀመሩን አስታውቋል።

የድርጅቱ መስራች እና ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አንበሱ ቶላ እንዳሉት ይህ ባለብዙ ዘርፍ የአስቸኳይ ጊዜ ምላሽ ፕሮጀክት በጤና፣ በሥርዓተ-ምግብ እና በንፁህ መጠጥ ውሃ ዘርፎች ላይ ያተኮረ ነው።ፕሮጀክቱ 4.5 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በጀት የተመደበለት ሲሆን ለዚህም በአሜሪካ መንግሥት የሚደገፈው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ ፈንድ (EHF) ድጋፍ አድርጓል።

የፕሮጀክቱ ዋና ግብ በኦሮሚያ ክልል 5 ዞኖች በተመረጡ 7 ወረዳዎች ውስጥ ለሚገኙ 295 ሺህ ገደማ የሚሆኑ ተጋላጭ የኅብረተሰብ ክፍሎችን፤ በችግር ምክንያት የሚከሰቱ የህመም እና የሞት መጠኖችን ፈጣን እና የተቀናጀ ምላሽ በመስጠት መቀነስ መሆኑን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል፡፡

ፈያ ኢንተግሬትድ ዴቬሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን ከ24 ዓመታት በላይ ለተቸገሩ ወገኖች የደረሰ ሀገር በቀል የልማት ድርጅት ሲሆን፤ የዛሬውን ከ295 ሺህ በላይ ወገኖች ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክት ይፋ ያደረገው 17ኛ ጠቅላላ ጉባዔውን እያደረገ ባለበት ወቅት ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...

መረጃ በማይሰጡ ኃላፊዎች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ የሚያስችል ሕግ ተዘጋጀ

የመገናኛ ብዙሃን እና የመረጃ ነፃነት የየራሳቸው ባህሪ ቢኖራቸውም እስካሁን...