የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የሀንጋሪው ጠቅላይ ሚኒስትር ለዋሽንግተን ብሄራዊ ጥቅም እንደሚያስፈልጉ አሳወቁ።
ቪክቶር ኦርባን የፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን አጋር መሆናቸውም ይታወቃል።
ከፕሬዚዳንት ትራምፕ ጋርም ፖለቲካዊ መግባባቱ አላቸው ኦርባን።
ዋሽንግተን በመጭው የሀንጋሪ ፓርላሜንታዊ ምርጫ ለጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ዖርባን ድጋፍ እንደምታደርግም ሩቢዮ ይፋ አድርገዋል።
ይሄኛው የአሜሪካ አቋም ከአውሮፓ ህብረት ፍላጎት ያፈነገጠና ለሩሲያ እንደበጎ ዜና የሚወሰድ ነው ተብሏል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ኦርባን ከትራምፕ ጋር ያላቸው የግል ግንኙነትም “ወርቃማው ዘመን “ ላይ የደረሰ ነው ይባልላቸዋል።
“ይህች አገር በመልካም ሁኔታ እንድትቀጥልና እንድትሰራ እንሻለን፤በእኛ ብሄራዊ ጥቅም ልክ ያለች ናት ፤በተለይም ርሶ ጠቅላይ ሚኒስትርና የአገሪቱ መሪ ሆነው እስከዘለቁ ድረስ”በሚል ለኦርባን ሩቢዮ ነግረዋቸዋል።
ማርኮ ሩቢዮ በቡዳፔስት ሀንጋሪ የጋራ ጋዜጣዊ መግለጫም ሰተዋል።
ዘገባው የአር ቲ ነው
