ትራምፕ ኢራን ያበለጸገችውን ዩራኒየም ለማስረከብ ተስማምታለች አሉ

Date:

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ያበለጸገችውን ዩራኒየም ለማስረከብ መስማማቷን ተናገሩ።

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል እየተካሄደ በነበረው የሰላም ድርድር ላይ ካላግባቡ ነጥቦች መካከል ቴህራን ያበለጸገችው ዩራኒየም አንዱ ነበር።

ፕሬዚዳንቱ በሳምንቱ መጨረሻ በዋሺንግተን እና በቴህራን መካከል ንግግር ሊቀጥል እንደሚችል ተናግረው፤ ከስምምነት ልንደርስ “በጣም ተቃርበናል” ብለዋል።

ትራምፕ በላስቬጋስ በአሜሪካ ምጣኔ ኃብት ላይ ባተኮረ ጉባዔ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ጦርነቱ “ያለምንም እንከን” እየሄደ እንደሆነ ተናግረው በቅርቡ ማብቃት አለበት ብለዋል።

ቀደም ሲል ዋይት ሐውስ ኢራን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንደማይኖራት መስማማቷን ገልጾ ነበር።

አክሎም ባለፈው ዓመት እስራኤል እና አሜሪካ የፈጸሙትን ድብደባ ተከትሎ ከመሬት በታች እንደተቀበረ የሚታመነውን የበለጸገ ዩራኒየም “የኒውክሌር አቧራ” አራግፈው ቆፍረው እንደሚያወጡ ተናግረው ነበር።

ትራምፕ በቀጣይ ዙር በሚደረገው የሁለቱ አገራት ድርድር እርግጠኛ ሆነው ታይተዋል።

ነገር ግን ከአምስት ቀናት በኋላ የሚያበቃው የተኩስ አቁም ስምምነቱ ስለመራዘሙ እርግጠኛ አለመሆናቸውን ጨምረው ተናግረዋል።

BBC

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...