ቻይና 500 ሚሊዮን ዶላር ለዓለም ጤና ድርጀት እንደምትለግስ ቃል ገባች

Date:

ቻይና በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ለዓለም ጤና ድርጅት 500 ሚሊዮን ዶላር ለመስጠት ቃል ገብታለች፡፡

ይህም ቻይና ለዓለም ጤና ድርጅት ድጋፍ ከሚያደርጉ ሀገራት ውስጥ በቀዳሚነት እንድትቀመጥ ያደርጋታል።

አሜሪካ ከዓለም ጤና ድርጅት አባልነት ራሷን ማግለሏን ተከትሎ ታደርገው የነበረው ድጋፍ በማቋረጡ ቻይና ትልቋ ለጋሽ ሀገር ሆናለችም ነው የተባለው።

ቻይና ይህንን ሀሳብ ያቀረበችው በጄኔቭ እየተካሄደ በነበረው አለም አቀፍ የጤና ጉባኤ ላይ ሲሆን ድጋፉ ቻይና ከሌሎች ሀገራት ጋር በጋራ ለመስራት ያላትን አቋም የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የዓለም የጤና ድርጅት አቅዶት የነበረውን የ2026 በጀት በ21 በመቶ በመቀነስ ወደ 4.2 ቢሊዮን ዶላር ዝቅ ያደረገ ሲሆን ይህም በዋናነት በትራምፕ አስተዳደር በተወሰደው እርምጃ ምክንያት የገንዘብ እጥረት በማጋጠሙ ነው ተብሏል።

የቻይና ውሳኔ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተሰሚነቷ ለመጨመር እያደረገቸው ካሉ ተግባራቶች እንደ አንዱ ሊወሰድ እንደሚችልም የዋሽንግተን ፖስት ዘገባ አመልክቷል፡፡

አሜሪካ ከዓለም ጤና ድርጅት መገለሏን ተከትሎ ቻይና እያደረገች ያለው እንቅስቃሴ በዓለም የጤና ሴክተር፣ አየር ንብረት ለውጥ እና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የላትን ተጽዕኖ እንደሚያሳድግላትም ተነግሯል።

(EBC)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...