ቻይና የዶክትሬት (PhD) ድግሪ አሰጣጥ ላይ አብዮት ፈጠረች!

Date:

ቻይና በዶክትሬት (PhD) ትምህርት ዘርፍ ትልቅ ለውጥ በማምጣት፣ እጩ ዶክተሮች ረጅም የጥናት ጽሁፍ (Thesis) ከማቅረብ ይልቅ ተግባራዊ የፈጠራ ውጤቶችን በማልማት ድግሪያቸውን እንዲያገኙ ልትፈቅድ መሆኑ ተሰማ።

ይህ እርምጃ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከንድፈ-ሀሳብ ባለፈ ለተግባራዊ ምርምር እና ለዓለም አቀፍ የፈጠራ ውጤቶች ትኩረት እንዲሰጡ ለማድረግ የታለመ ነው።

እንደ ኢንጂነሪንግ እና ቴክኖሎጂ ባሉ የሳይንስ ዘርፎች ተማሪዎች የጥናት ሰነድ ከማዘጋጀት ይልቅ ለገበያ የሚውሉ ቴክኖሎጂዎችን ወይም አዳዲስ የፈጠራ ውጤቶችን (Prototypes) በማሳየት ብቃታቸውን እንዲያረጋግጡ ዕድል ይሰጣቸዋል።

ይህ አዲስ አቅጣጫ በትምህርት እና በኢንዱስትሪ መካከል ያለውን ክፍተት በማጥበብ ለሀገር ኢኮኖሚ ፈጣን እድገት አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሎ ታምኖበታል።

ምንም እንኳን አንዳንድ ምሁራን የንድፈ-ሀሳብ ምርምር መሰረታዊ ሳይንስ እንዳይጎዳ ቢሰጉም፣ አብዛኛው ደጋፊ ግን የከፍተኛ ትምህርት ውጤት በወረቀት ላይ ብቻ ሳይሆን በተጨባጭ ለውጥ ላይ መመስረት አለበት በማለት ድጋፋቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።

ይህ አሰራር በስፋት ተግባራዊ ከሆነ ከፍተኛ ትምህርት ለኢኮኖሚ ልማትና ለፈጠራ ግቦች የሚኖረውን ሚና ሙሉ በሙሉ የሚቀይር ይሆናል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...