“ቻይናና አሜሪካ ተስማሙ?

Date:

ቻይናና አሜሪካ ለተጨማሪ ዘጠና ቀናት ታሪፍ ላለመጨመር ተስማምትዋል ተባለ። በዓለም በባለግዙፍ ኢኮኖሚዎቹ መካከል የተፈጠረው የታሪፍ ውጥረት አደጋ ይዞ ይመጣል በሚል ውይይቶች ሲደረጉ ቆይተዋል።

ቤይጂንግና ዋሽንግተን ተጨማሪ ታሪፍ እርስበርስ ”ሊጣጣሉ ” የመጨረሻው ቀን ላይ ደርሰው ነበር።

ለተጨማሪ ሶስት ወራት ታሪፍን ላለመጣል አስቀምጠውት የነበረውን ቀነ ገደብ አራዘሙት የሚል መረጃ ቅድሚያ በሲ ኤን ቢ ሲ በኩል የወጣ ሲሆን ይህም የዓለምን ኢኮኖሚ በተወሰነ መጠን ያረጋጋዋል የሚል ተስፋ ተጥሎበታል።

አገራቱ ባይስማሙ ኖሮ አሜሪካ ከቻይና በምታስገባቸው ምርቶች ላይ ከ30 በመቶ ወደ 64 በመቶ ታርፉን ከፍ ለማድረግ ትገደድ ነበር።

ቻይና በአሜሪካ ላይ ምን ያህል ታሪፍ ልትጥል እንደምትችል ግን የታወቀ ነገር አልነበርም።

በእርግጥ በአሁኑ ሰዓት ቤይጂንግ ከዋሽንግተን በምታስገባቸው ምርቶች ላይ አስር በመቶ ታሪፍ እንደጣለች ይታወቃል።

ከዋይት ሀውስ ወጣ የተባው የተስፋ መረጃ ይፋ የሆነው ዶናልድ ትራምፕ ከ90 በላይ አገራት ላይ ታሪፍ በጣሉ ማግስት ነው።

ሲ ኤን ኤንና ሲ ኤን ቢ ሲ ኒውስ ዘግበውታል።

NBCEthiopia

ሆኖ_መገኘት

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...