“አረቢካ ቡና” የሚለው ስያሜ “የኢትዮጵያ ቡና” ተብሎ እንዲቀየር ተጠየቀ

Date:

ኢትዮጵያ የቡና መገኛ በመሆኗ ለታሪክና ለሳይንሳዊ አስተዋፅኦ እውቅና ለመስጠት የስያሜ ለውጥ እንዲደረግ ተመራማሪው ሰሎሞን ተክሌ ጥሪ አቅርበዋል።

መገኛው ኢትዮጵያ የሆነው “አረቢካ ቡና” እውነተኛ ምንጩን የሚያንፀባርቅ ስያሜ ያስፈልጋል ብለዋል።

በሌላ በኩል፤ ሌሎች ሀገራት የቡና መገኛ ነን በማለት የሚያቀርቡትን መረጃ አልባ መከራከሪያ ነቅፈዋል።

ተመራማሪው በተጨማሪም የኢትዮጵያ ባለሥልጣናትና ባለድርሻ አካላት ኢትዮጵያ የቡና መገኛ መሆኗን በሳይንሳዊ መንገድ በማረጋገጥ በዩኔስኮ እውቅና ለማስገኘት እንዲሠሩ አሳስበዋል።

“ታሪካዊና ሳይንሳዊ ምንጮች ቡና ከኢትዮጵያ የተገኘ መሆኑን በግልጽ ያሳያሉ” ሲሉ ተመራማሪው ለሀገር ውስጥ ሚዲያ መናገራቸውን ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...