በእንግሊዝ ሊግ ካፕ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ አርሰናል ብራይተንን 2 ለ 0 በማሸነፍ ለሩብ ፍጻሜ ደረወሷል።
አሰልጣኝ ሚካኤል አርቴታ 10 ቋሚ ተሰላፊ ተጫዋቾችን ቀይሮ ወደ ሜዳ በገባበት ጨዋታ አሁንም ግብ ሳይቆጠርበት ወጥቷል።
በኢምሬትስ በተደረገው ጨዋታ ንዋኔሪ እና ተቀይሮ የገባው ቡካዮ ሳካ የመድፈኞቹን የማሸነፊያ ግቦች አስቆጥረዋል።
ሊቨርፑል በሜዳው ክሪስታል ፓላስን ባስተናገደበት ጨዋታ 3 ለ 0 ተሸንፎ ከውድድሩ ውጭ ሆኗል።
በአንፊልድ በተደረገው ጨዋታ ኢስማኤል ሳር የፓላስን ሁለቱ ግቦች ሲያስቆጥር የርሚ ፒኖ 3ኛዋን ግብ አስገኝቷል።
ሆላንዳዊው አሰልጣኝ አርን ስሎት ካደረጓቸው ያለፉት ሰባት ጨዋታዎች በስድስቱ ለመሸነፍ ተገደዋል።
በሌሎች ጨዋታዎች ማንችስተር ሲቲ ስዋንሲ ሲቲን 3 ለ 1አሸንፏል።
