አየር መንገዱ ሦስት አዳዲስ የአገር ውስጥ አውሮፕላን ማረፊያዎችን ሊያስመርቅ ነው

Date:

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በግንባታ ላይ ከሚገኙት የአገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያዎች መካከል ሦስቱ ተጠናቀው በሚያዚያ ወር አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ አስታወቀ።

አየር መንገዱ ባወጣው መረጃ መሠረት፣ የአገሪቱን የአየር ትራንስፖርት ተደራሽነት ለማስፋፋት እየተገነቡ ካሉ ፕሮጀክቶች ውስጥ ነገሌ ቦረና ፣ ጎሬ መቱ ፣ ደብረ ማርቆስ ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው በመጪው ሚያዚያ ወር 2018 ዓ.ም ይመረቃሉ።

አዳዲሶቹ ማረፊያዎች የንግድ እና የማኅበራዊ ትስስርን ከማጠናከራቸው ባለፈ፣ ለተጓዦች አማራጭና ቀልጣፋ ትራንስፖርት ለማቅረብ ያለሙ ናቸው።

አየር መንገዱ ከእነዚህ ሦስት ማረፊያዎች በተጨማሪ ሌሎች የኤርፖርት ግንባታዎችንና የማስፋፊያ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

“የእነዚህ አየር ማረፊያዎች መጠናቀቅ አየር መንገዱ ያለውን የአገር ውስጥ በረራ መዳረሻዎች ቁጥር ከማሳደጉም በላይ፣ ለየአካባቢው ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል” ሲል አየር መንገዱ አመልክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...