የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደንበኞቹን ረጅም ርቀት ለማጓጓዝ የሚያስችለውን አራተኛውን ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን ዛሬ ተረክቧል፡፡
አየር መንገዱ የተረከበው አዲሱ ኤርባስ አውሮፕላን፤ የኢትዮጵያን ገፅታ በአዲስ ዕይታ ከፍ የሚያደርግ መሆኑን አስታውቋል፡፡
አየር መንገዱ አሁን ላይ እጅግ ዘመናዊ 4 ኤርባስ A350-1000 እና 20 ኤርባስ A350-900XWB አውሮፕላኖች ባለቤት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡
