ኢራን 3,800 ኪሎ ሜትር በሚርቀው የአሜሪካ እና ዩኬ የጦር ሰፈር ላይ ሚሳዔል አስወነጨፈች

Date:

ኢራን፤ ዲዬጎ ጋርሺያ በተባለው የአሜሪካ እና የዩናይትድ ኪንግደም ጋራ የጦር ሰፈር ላይ ሁለት መካከለኛ ርቀት ተወንጫፊ ባለስቲክ ሚሳዔሎችን መተኮሷን የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።

ዎል ስትሪት ጆርናል ጋዜጣ በርካታ ምንጮችን ጠቅሶ ባወጣው ዘገባ፤ የተተኮሱት ሁለቱም ሚሳዔሎች በሕንድ ውቅያኖስ ላይ የሚገኘውን ጦር ሰፈር እንዳልመቱት አስታውቋል።

ሴኤንኤን በበኩሉ፤ ሚሳዔሎቹ የተተኮሱት በአካባቢው ሰዓት አቆጣጠር አርብ ንጋት ላይ እንደሆነ ከአሜሪካ ባለሥልጣን መስማቱን ዘግቧል።

ከኢራን እስከ ዲዬጎ ጋርሺያ ያለው ርቀት 3,800 ኪሎ ሜትር ገደማ ነው። የቀድሞው ኢራን ጠቅላይ መሪ የአገሪቱ ሚሳዔል የሚወነጨፍበት ርቀት ከ2,000 እንዳይበልጥ ትዕዛዝ ሰጥተው ነበር።

ቢቢሲ ስለ ጥቃቱ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ለአሜሪካ ፔንታገን እና ለዩናይትድ ኪንግደም መከላከያ ሚኒስቴር ጥያቄ አቅርቧል። የአሜሪካው መከላከያ ሚኒስቴር ፔንታጎን “በአሁኑ ሰዓት ማቅረብ የሚችለው ምንም ነገር እንደሌለ” ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ምርጫ ለሰላም ግንባታ

ግዮን መጽሔት :-ለኢትዮጵያ ሰላም ምርጫ አማራጭ የሌለው መንገድ ነው።...

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...