ኢራን በሆርሙዝ የሚያልፉ መርከቦች ላይ ላለመተኮስ በይፋ ቃል ትግባ

Date:

ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥ እንደሚከፈት እና በወሽመጡ የሚያልፉ መርከቦች ላይ ጥቃት እንደማታደርስ በይፋ ቃል እንድትገባ እንደምትፈልግ አሜሪካ አስታወቀች።

የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ማንነታቸው ያልተገለጸ ባለሥልጣንን ጠቅሰው እንደዘገቡት፤ ቴህራን ለፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አማካሪዎች በግል በሰጠችው ማብራሪያ መርከቦች ላይ መተኮሷ ስህተት መሆኑን አምናለች።

ኢራን ጥቃቱ የተፈጸመው ከቁጥጥር ውጭ በሆኑ ውስጣዊ ኃይሎች መሆኑን አስታውቃለች።

ባለፉት ቀናት የተኩስ ልውውጥ ቢያደርጉም ሁለቱም ወገኖች ንግግራቸውን ለመቀጠል መስማማታቸውን ትራምፕ ተናግረዋል።

ኢራን እና አሜሪካ የፈረሙት የመግባቢያ ሰነድ፤ ቴህራን በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል የሚያልፉ መርከቦች ደኅንነታቸው እንዲጠበቅ ታደርጋለች።

ከሰሞኑ የተነሳው ግጭት የመግባቢያ ሰነዱን ያፈረሰ መሆኑን ሁለቱም አገራት ገልጸዋል።

በኢራን እና በአሜሪካ መካከል የሚደረገው ድርድር እንዲቀጥል መስማማታቸውን የገለጹት ትራምፕ፤ ቀደም ሲል የነበረው የተኩስ አቁም ስምምነት ግን ማብቃቱን ለቴህራን ማሳወቃቸውን ተናግረዋል።

ቴህራን በመሠረተ ልማቶቿ ላይ ጥቃት የሚፈጸም ከሆነ አጸፋውን እንደምትመልስ አስጠንቅቃለች።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጠቅላይ መሪ ለአባታቸው ግድያ “የበቀል እርምጃ” እንደሚወሰድ ተናገሩ

የኢራን ጠቅላይ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ በጽሑፍ ባስተላለፉት መልዕክት አባታቸው...

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የመጨረሻ ልምምዱን ሰርቷል

ቡድኑ ነገ የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ዙር የመልስ ጨዋታውን...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ለመደራደር አለመጠየቋን አስታወቀች

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ፤ አገራቸው...

ሱዳን ዉስጥ ለሦስት ዓመታት የተካሄደው ጦርነትን ሰለ ማቆም

የሱዳን ብሔራዊ ጦር ለሦስት ዓመታት የተካሔደውን ጦርነት ለማቆም አሜሪካ...