ኢትዮጵያ ከ50 በላይ ሀገራት የሚሳተፉበትን የሆርቲፍሎራ ኤክስፖ ልታስተናግድ ነዉ

Date:

10ኛው ዓለምአቀፍ የሆርቲካልቸር የንግድ ትርዒት (ሆርቲፍሎራ ኤክስፖ 2026) ከመጋቢት 15 እስከ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እንደሚካሄድ ተገለጠ።

የፍራፍሬ አምራችና ላኪዎች ማኅበር ከኤች.ፒ.ፒ. ኤግዚቢሽን ወርልድዋይድ ጋር በመተባበር የሚያዘጋጁት ይህ ታላቅ ሁነት በዘርፉ የተሰማሩ በርካታ አካላትን በአንድ ጣሪያ ስር ያሰባስባል ተብሏል።

በንግድ ትርዒቱ ላይ ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ከተውጣጡ ከ50 በላይ ሀገራት የሚመጡ ከ150 በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ አልሚ ባለሀብቶች፣ አምራቾች፣ የዘርና የቴክኖሎጂ አቅራቢዎች እንዲሁም የፋይናንስና የሎጅስቲክስ ተቋማት ይሳተፋሉ።

ይህ መድረክ ምርትና አገልግሎትን ለማስተዋወቅ ብቻ ሳይሆን፣ በኢንዱስትሪው ዘላቂ ልማት፣ በቴክኖሎጂ ፈጠራና በዓለምአቀፍ የገበያ ትስስር ዙሪያ ጠቃሚ ምክክሮች የሚደረጉበት መሆኑ ተጠቁሟል።

የዘንድሮው ኤክስፖ ልዩ የሚያደርገው፣ የግብርና ሚኒስቴር የ10 ዓመቱን ብሔራዊ የሆርቲካልቸር ልማት ስትራቴጂ እና የ15 ዓመቱን የአቮካዶ ልማት መርሃግብር ይፋ ካደረገ በኋላ የሚካሄድ የመጀመሪያው ግዙፍ ዓለምአቀፍ ሁነት በመሆኑ ነው።

በቆይታውም በምግብ ደህንነት፣ በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) አጠቃቀም፣ በባህር ጭነትና በዘላቂ ፋይናንስ ዙሪያ ያተኮሩ ውይይቶች እንደሚካሄዱ ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...