ኤልሳቤጥ ወልደጊዮርጊስ (ዶ/ር) ከዚህ አለም በሞት ተለዩ

Date:

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር በመሆን ያገለገሉት ኤልሳቤጥ ወልደጊዮርጊስ(ዶ/ር) ከዚህ አለም በሞት ተለዩ፡፡

በኮኔል ዩኒቨርሲቲ እና በኒውዮርክ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ ትምህርታቸውን የተከታተሉት ዶ/ር ኤልሳቤጥ በሸገር ሬዲዮ በ #ሸገር_ካፌ ፕሮግራም በሥነ ጥበብና ታሪክ ጉዳዮች ላይ በተደጋጋሚ በመቅረብ እውቀታቸውን አካፍለዋል፡፡

ለስራ ከቆዩበት በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ሻርጃ ከተማ ማረፋቸው ተሰምቷል፡፡

የዶ/ር ኤልሳቤጥ አስከሬን ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ሰምተናል፡፡

ለዶ/ር ኤልሳቤጥ ወልደጊዮርጊስ ወዳጅ ዘመዶች ሸገር መፅናናትን ይመኛል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እስከ አምስት ዓመት እስራት የሚያስቀጡ የመረጃ ነጻነት አዋጅ ጸደቀ

ለ15 ዓመታት በስራ ላይ ከቆየው “የመገናኛ ብዙኃንና የመረጃ ነፃነት...

በደቡብ አፍሪካ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን የተላለፈ ማስጠንቀቂያ

በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ኢምባሲ በሀገሪቱ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ እየተከታተለና...

በበጀት አመቱ 22.9 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ እየተሠራ ነው

ከታቀደው 22 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዶላር ኩንታል እስካሁን  20...

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...