የ2025 ግሎባል ሀንገር ኢንዴክስ ይፋ ሆነ

Date:

የሀገራትን የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ደረጃ የሚገመግመው የ’2025 ግሎባል ሀንገር ኢንዴክስ’ ጥናት በአፍሪካ ህብረት ዋና መሥሪያ ቤት በይፋ ተመርቋል።

በጥናቱ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ እንደተገለጸው፣ ዓለም ባለፉት ዓመታት በርሀብ ቅነሳና በምግብ ዋስትና ረገድ ተስፋ ሰጪ ስኬቶችን አስመዝግቦ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን ከፍተኛ መሰናክሎች ተደቅነውበታል።

በተለይም በየአካባቢው የሚቀሰቀሱ ግጭቶች፣ እየተባባሰ የመጣው የአየር ንብረት ለውጥ እንዲሁም ተያያዥ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ቀውሶች የዘርፉን ጥረቶች እንዲጓተቱ ማድረጋቸው ተመላክቷል።

በመሆኑም ይህንን ፈታኝ ወቅት ለማለፍና የተጋረጡ ስጋቶችን ለመቀልበስ፣ በዘርፉ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች በአዲስ ቁርጠኝነትና ስልታዊ በሆነ አመራር ሊደገፉ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።

ወቅታዊው ሪፖርት ሀገራት የረሀብን አዙሪት ለመስበር ፖሊሲዎቻቸውን እንዲከልሱና ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ የሚያሳስብ ጠንካራ መልዕክት አስተላልፏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...