የብሔራዊ ባንክ መመሪያ ማሻሻያ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በውጭ ምንዛሪ መመሪያው ላይ ባደረገው አዲስ ማሻሻያ፣ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ለሥራ ማስጀመሪያነት በዝግ ሒሳብ አስይዘውት የነበረው 30 ሚሊዮን ብር እንዲመለስላቸው ወሰነ።

ይህ ውሳኔ በአሁኑ ወቅት ወደ ሥራ የገቡ 13 የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች የገጠማቸውን የካፒታል እጥረት ለመቅረፍና የሥራ እንቅስቃሴያቸውን ለማቀላጠፍ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።

ቢሮዎቹ ፈቃድ በሚያወጡበት ወቅት ይህን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ማስያዝ ግዴታ ሆኖባቸው የቆየ ቢሆንም፣ አዲሱ ማሻሻያ ግን ቢሮዎቹ ገንዘቡን አንቀሳቅሰው ለገበያ ትስስርና ለዕለታዊ ግብይት እንዲያውሉት ዕድል ሰጥቷቸዋል።

የዘርፉ ተዋንያን የተደረገው ማሻሻያ አበረታች መሆኑን ገልጸው፣ በቀጣይም የውጭ ምንዛሪ ገበያውን ይበልጥ ነፃና ተወዳዳሪ የሚያደርጉ ተጨማሪ ማሻሻያዎችን እንደሚጠብቁ ጠቁመዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...