የሰቆጣ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽ/ቤት የትራኮማ መከላከያ የመድሀኒት እደላ ዘመቻ ከሐምሌ 6 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ለተከታታይ 7 ቀን እየሰጠ እንደሚገኝ አስታውቋል ።
ዘመቻው ማንኛውም በከተማ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን የሚያሳትፍ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዘመቻው ከ47ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተደራሽ እንደሚያደርግ ጤና ጽ/ቤቱ አስታውቋል።
ከዘመቻውም ጎን ለጎንም ማንኛውም ከ15 ዓመት በላይ የሆነ የከተማዋ ነዎሪዎች የዓይን ፀጉር መቀልበስ ልየታ እየተሰራ ሲሆን የዓይን ጸጉር መቀልበስ ችግር ያለባችሁ ህክምናው የሚሰጥ መሆኑን አውቀው ህክምናውን እንዲያገኙ ጽ/ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።
በተጨማሪም ለዘመቻው መሳካት የከተማው ማህበረሰብ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ሲል ጤና ተቋሙ መጠየቁን ብስራት ከሰቆጣ ከተማ ኮሙኒኬሽን ያገኘው መረጃ ያሳያል::
