የነዳጅ ግብይት ሥርዓትና የመንግሥት የቁጥጥር እርምጃ

Date:

በዓለም አቀፍ ደረጃ በመካከለኛው ምስራቅ በተከሰተው ግጭት ሳቢያ የነዳጅ አቅርቦት መዛባትና የዋጋ ንረት እያጋጠመ ባለበት በዚህ ወቅት፣ በኢትዮጵያም መንግሥት የዋጋ ማስተካከያ ማድረጉ ይታወቃል።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሺዴ በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት፣ መንግሥት ለነዳጅ አቅርቦት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ድጎማ እያደረገ ቢሆንም፤ ነዳጅን ከተቀመጠለት የዋጋ ተመን በላይ በመሸጥ ህገ-ወጥ ትርፍ ለማካበት የሚጥሩ አካላት መበራከታቸውን በጥናት ተረጋግጧል።

ይህንን ተከትሎም፣ ህገ-ወጥ ድርጊቱን የፈጸሙ የግል ነጋዴዎችንና የመንግሥት ተቋማትን ጨምሮ ተባባሪ የሆኑ አካላትን በቁጥጥር ስር የማዋል ሰፊ የሕግ ማስከበር ዘመቻ ተጀምሯል።

ሚኒስትሩ አክለውም፣ በዓለም ገበያ ካለው ከፍተኛ ጭማሪ አንጻር የተደረገው የዋጋ ማስተካከያ አነስተኛ መሆኑን ጠቁመው፣ በቀጣይም የቁጠባ ግብይት ሥርዓት ተግባራዊ እንደሚደረግ ገልጸዋል።

በመሆኑም ሕዝቡ ይህንን ሕገ-ወጥ ንግድ በመከላከል ረገድ ከመንግሥት ጎን እንዲቆም ጥሪ ቀርቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...