ኢትዮጵያ ዉስጥ በአማራ ክልል የሚደረገዉ ግጭት የክልሉን የጤና አገልግሎት ክፉኛ ማወኩን ድንበር የለሽ ሐኪሞች (MSF-በፈረንሳይኛ ምሕጻሩ) የተሰኘዉ ግብረ-ሠናይ ድርጅት አስታወቀ።
ዓለም አቀፉ የሕክምና አገልግሎት ድርጅት ዛሬ እንዳስታወቀዉ ግጭቱ ከፍተኛ የመድሐኒት እጥረት አስከትሏልም።
የኢትዮጵያ መንግሥት ኃይላትና በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፋኖ ታጣቂዎች የሚያደርጉት ግጭት የክልሉን ሕዝብ እንቅስቃሴ በጅጉ አዉኮታል።
ድንበር የለሽ ሐኪሞች እንዳለዉ የካላ-አዛር (Leishmaniasis ወይም ቁንጭር) በሽታንና በእባብ መነደፍ የሚደርሰዉን ሕመም ለማከም የሚረዱ መድሐኒቶች ማግኘት ሲበዛ ከባድ ነዉ።
ድርጅቱ እንዳለዉ በክልሉ የሚገኙ የጤና ተቋማት የሚሰጡት አገልግሎት የቀነሰ ሲሆን በቂ መድሐኒትም የላቸዉም።
በግጭቱ ምክንያት ዓለም አቀፉ የሕክምና ግብረ-ሠናይ ድርጅት MSF ለፅኑ ሕሙማን ይሰጥ የነበረዉን የአምቡላስ ሕክምና አገልግሎት ማቋረጡን አስታዉቋልም።
