የአፍሪካ ህብረት አዲሱ የአሜሪካ ታሪፎች የአስርተ አመታት የንግድ ትብብርን አደጋ ላይ ይጥላሉ አለ

Date:

የአፍሪካ ህብረት እንዳስታወቀው በአህጉሪቱ ላይ በአሜሪካ የተጣሉ አዲሶቹ ታሪፎች የአስርተ አመታት የዘለቀውን “በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ የንግድ እና የትብብር” ግንኙነትን አደጋ ላይ እንደሚጥሉ አስጠንቅቋል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ማሃሙድ አሊ የሱፍ የአሜሪካ መንግስት በወሰደው የጣሪፍ ጭማሪ ላይ ያላቸውን ጥልቅ ስጋት በመግለጽ ይህንንም ውሳኔ እንደገና እንዲያጤነው አሳስበዋል።

አሜሪካ የረዥም ጊዜ እሴቶች እና በጋራ ምኞቶች ላይ የተመሰረተውን የረጅም ጊዜ አጋርነት ከማጠናከር ይልቅ ማዳከም ተገቢ አይደለም ማለታቸው ተነግሯል።

በተለይም እንደ ትልቅ የጨርቃ ጨርቅ ላኪ የሆነችው ሌሶቶ እስከ 50 በመቶ የሚደርስ ታሪፍ የተጣለባት ሲሆን ደቡብ አፍሪካ፣ ማዳጋስካር እና ቦትስዋና ደግሞ ከ 30 በመቶ በላይ በሆነ የታሪፍ ጭማሪ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እስከ አምስት ዓመት እስራት የሚያስቀጡ የመረጃ ነጻነት አዋጅ ጸደቀ

ለ15 ዓመታት በስራ ላይ ከቆየው “የመገናኛ ብዙኃንና የመረጃ ነፃነት...

በደቡብ አፍሪካ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን የተላለፈ ማስጠንቀቂያ

በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ኢምባሲ በሀገሪቱ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ እየተከታተለና...

በበጀት አመቱ 22.9 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ እየተሠራ ነው

ከታቀደው 22 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዶላር ኩንታል እስካሁን  20...

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...