የአፍሪካ ህብረት አዲሱ የአሜሪካ ታሪፎች የአስርተ አመታት የንግድ ትብብርን አደጋ ላይ ይጥላሉ አለ

Date:

የአፍሪካ ህብረት እንዳስታወቀው በአህጉሪቱ ላይ በአሜሪካ የተጣሉ አዲሶቹ ታሪፎች የአስርተ አመታት የዘለቀውን “በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ የንግድ እና የትብብር” ግንኙነትን አደጋ ላይ እንደሚጥሉ አስጠንቅቋል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ማሃሙድ አሊ የሱፍ የአሜሪካ መንግስት በወሰደው የጣሪፍ ጭማሪ ላይ ያላቸውን ጥልቅ ስጋት በመግለጽ ይህንንም ውሳኔ እንደገና እንዲያጤነው አሳስበዋል።

አሜሪካ የረዥም ጊዜ እሴቶች እና በጋራ ምኞቶች ላይ የተመሰረተውን የረጅም ጊዜ አጋርነት ከማጠናከር ይልቅ ማዳከም ተገቢ አይደለም ማለታቸው ተነግሯል።

በተለይም እንደ ትልቅ የጨርቃ ጨርቅ ላኪ የሆነችው ሌሶቶ እስከ 50 በመቶ የሚደርስ ታሪፍ የተጣለባት ሲሆን ደቡብ አፍሪካ፣ ማዳጋስካር እና ቦትስዋና ደግሞ ከ 30 በመቶ በላይ በሆነ የታሪፍ ጭማሪ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...

አዲስ አበባ፦ የዜጎች ቀይ መስመር!

(የግል አስተያየት) አዲስ አበባ የኢትዮጵያውያን መናገሻ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች ለዘመናት...

አብን የምክክሩን ውጤት ውድቅ አደረገ!

አብን በሀገራዊ ምክክሩ ማጠቃለያ ላይ የተፈጸመውን “ሕገ-ወጥ ጣልቃ-ገብነት” በመቃወም...