የኢራን አብዮታዊ ዘብ በአገሪቱ ላይ ሊቃጣ የሚችል ወደታራዊ ጥቃትን ለመከላከል ያለውን ዝግጁነት ለመፈተሽ ቁልፍ በሆነው የሆርሙዝ ሰርጥ ልምምድ ማድረግ መጀመሩን አስታወቀ።
ይህ ወታደራዊ ልምምድ መካሄድ የጀመረው በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ሁለተኛ ዙር ድርድር ጄኔቭ፣ ስዊትዘርላንድ ውስጥ ሊካሄድ በተቃረበበት እና አሜሪካ በኢራን አቅራቢያ ግዙፍ ወታደራዊ መርከቦቿን እያጠናከረች ባለበት ጊዜ ነው።
ለድርድር ወደ ጄኔቭ ያመሩት የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ፤ ኢራን ለማስፈራሪያ እንደማትንበረከክ በመግለጽ “ትክክለኛ፣ ፍትሐዊ እና ሚዛናዊ ስምምነት” እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ ኢራን እስካሁን ያዳበረችውን ለኒውክሌር ጦር መሣሪያ ሊውሉ የሚችሉ የዩራኒየም ውጤቶችን እና የማብላያ ማዕከላቷን በሙሉ ማስወገድ እንዳለባት አስጠንቅቀዋል።
