በዩናይትድ ስቴትስ፣ በእስራኤል እና በኢራን መካከል የተቀሰቀሰው ጦርነት በአዲሱ የዓለም ሥርዓት ውስጥ ከተካሄዱት ዋነኘው ሆኖ ሊታይ ይችላል።
በዚህ ሥርዓት ውስጥ ለአስርተ ዓመታት የዓለም አቀፍ ባህሪን የሚቆጣጠሩት ሕጎች የነበራቸውን ተጽዕኖ እያጡ ነው።
ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቂያ በኋላ ለረዥም ጊዜ፣ ጦርነት እና ዲፕሎማሲ የሚካሄዱት በዓለም አቀፍ ሕግ፣ በተባበሩት መንግሥታት እና በሌሎች ተቋማት በተቀረጹ ማዕቀፎች ውስጥ ነበር።
እነዚህ ደንቦች እና ስምምነቶች ለሚፈለገው ዓላማ እንዲውሉ ተደርገው ቢተረጎሙም፣ መንግሥታት እንቅስቃሴዎቻቸውን በአጠቃላይ በዚያ ሥርዓት ውስጥ ለማሳየት ይጥሩ ነበር።
ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች በተለምዶ በሕግ ክርክሮች፣ በዲፕሎማሲያዊ ምክክሮች ወይም በዓለም አቀፍ ጥምረት ምሥረታ የታጀቡ ነበሩ።
በዚህ ጦርነት ግን እነዚህ ጉዳዮች በጣም ውስን ሚና ብቻ ያላቸው ይመስላሉ።
