የኢትዮጵያ ማረሚያ ኮሌጅን ስራ ለማስጀመር የሰነድ ርክክብ ተደረገ

Date:

የኢትዮጵያ ማረሚያ ኮሌጅን የድህረ ምረቃ ዲፕሎማ ትምህርት ለማስጀመር በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሲዘጋጅ የቆየው ካሪኩለምና ሞጁል ስራ ተጠናቆ የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በይፋ ተረክቧል።

ኮሌጁን ስራ ለማስጀመር የሚያስችሉ ሰነዶችን የተረከቡት የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀኔራል የኑስ ሙሉ በአስተላለፉት መልዕክት የማረሚያ ሳይንስ ትምህርት በሃገራችን ብዙ እንዳልተሰራበት ገልጸው፣ ነገር ግን የየዕለት ስራዎች ጽናትን፣ ርህራሄን፣ ሰዎችን መርዳትንና ራስን አሳልፎ መስጠትን የሚጠይቁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ኮሚሽነር ጄኔራሉ አክለውም ኮሚሽኑ የተረከባቸው ሰነዶች በድህረ ምረቃ ዲፕሎማ ትምህርት በመጀመር በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል በማፍራት በፌዴራልና በክልል ማረሚያ ቤቶች ያለውን የሰው ኃይል ክፍተት ለመሙላት በከፍተኛ ደረጃ ያግዛሉ ብለዋል፡፡

ሰነዶችን ያስረከቡት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ታምራት ሙሉጌታም በአስተላለፉት መልዕክት የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽንን በተማረ የሰው ኃይል ለማጠናከር በዘርፉ የተሻለ ዕውቀትና ግንዛቤ ባላቸው ባለሙያዎች የኮሌጁ ስርዓተ ትምህርት በጥራት መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...