የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት ፈቃድ ሰጠ

Date:

የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ለማሳደግና የሎጅስቲክስ ዘርፉን ለማጠናከር በማለም ለሶስት ተጨማሪ ኩባንያዎች የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ የስራ ፈቃድ ሰጠ።

ፈቃድ የተሰጣቸው ኩባንያዎች ኢትዮ ሬል ሎጅስቲክስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር፣ ኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ትራንስፖርት አክስዮን ማህበር እና ገልፍ ኢንጎት ኤፍ ዜድ ሲ ኢንደስትሪስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ናቸው።

የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ እንደገለጹት (ዶ/ር) ፣ ተጨማሪ ኩባንያዎች ወደ ዘርፉ መግባታቸው በገበያው ውስጥ ፉክክርን በማነቃቃትና በትብብር በመስራት የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ ለማሳደግ አስተዋጽኦ ያደርጋል።

የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ በበኩላቸው፣ የመልቲ ሞዳል አገልግሎት ወጪን በመቀነስ እና የገቢ ዕቃዎች ደህንነትን በመጠበቅ በፍጥነት ወደ ተፈለገው ቦታ እንዲደርሱ እንደሚያግዝ ገልጸዋል።

በአጠቃላይ፣ የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት ዘርፉን የተቀላቀሉ ኦፕሬተሮች ቁጥር ወደ ሰባት አድጓል። በቅርቡ ዘርፉን የተቀላቀሉት ኦፕሬተሮች ፓናፍሪክ ግሎባል፣ ጥቁር አባይ ትራንስፖርት እና ኮስሞስ መልቲ ሞዳል ኦፕሬሽን የተሰኙ ኩባንያዎች መሆናቸዉ ይታወቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...