የኢትዮጵያ ብር ከዶላር ጋር ያለው የምንዛሪ ተመን በከፍተኛ ደረጃ መዳከሙ ታወቀ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባካሄደው የውጪ ምንዛሪ ጨረታ፣ የኢትዮጵያ ብር ከአሜሪካን ዶላር ጋር ያለው የምንዛሪ ተመን በከፍተኛ ደረጃ መዳከሙ ታውቋል። ይህ ለውጥ በተለይ ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ የገበያውን መረጋጋት ለመደገፍ በተዘጋጀው የጨረታ መድረክ ላይ የሚታይ ትልቅ ጭማሪ ነው።

ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በተካሄደው 11ኛዉ ዙር የውጪ ምንዛሪ ጨረታ፣ ለአንድ የአሜሪካን ዶላር አማካይ የምንዛሪ ተመን ብር 154.3993 ሆኖ ተመዝግቧል። በዚህ ዙር 17 ባንኮች የውጭ ምንዛሪ ድልድል ማግኘታቸውን ካፒታል ተመልክቷል።

ከአንድ ወር በፊት፣ ጥቅምት 04 ቀን 2018 ዓ.ም. በተካሄደው 10ኛዉ ዙር ጨረታ የአንድ ዶላር አማካይ ተመን 148.1007 ብር ነበር። ይህ ማለት ብሩ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በአማካይ 4.25% በዶላር ላይ መዳከምን አሳይቷል።

​ከሁለት ወራት በፊት በ9ኛው ዙር ጨረታ የተመዘገበው አማካይ ተመን 138.2 ብር እንደነበር ይታወሳል። ከዚህ ተመን ጋር ሲነፃፀር፣ የዶላር ዋጋው በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመር በሁለት ወራት ውስጥ የ11.72% የምንዛሪ ተመን ጭማሪ ታይቷል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ በጨረታ ማቅረቡን የገበያውን መረጋጋት ለመደገፍ ያለመ ቢሆንም፣ የብር ተመን ፈጣን መዳከም ግን የገንዘብ ገበያው ምን ያህል ፈጣን ለውጥ እያስተናገደ እንደሆነ የሚያሳይ መሆኑ ተጠቁሟል።

capital news

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...