የኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት ይዞታ እና የኢትዮጵያና ኤርትራ የቃላት ውዝግብ ያሳደረው ስጋት

Date:



የትግራዩ ጦርነት ካበቃ ሦስት ዓመት ቢጠጋም ትግራይአሁንም ለጋዜጠኞች አደገኛ መሆኗ ቀጥሏል ሲል ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት CPJ ትናንት አስታውቋል።

CPJ በተለይ ለተተኮሰባቸው፣ ለታሰሩ ድንገተኛ አሰሳም ለተካሄደባቸውና በአካባቢው እንደገና ግጭት ሊያስነሳ የሚችል የስልጣን ሽኩቻ ውስጥ ለሚዘግቡት ጋዜጠኞች ክልሉ ውጥረት የሰፈነበትና አደገኛም ነው ብሏል። CPJ ከዚህ ቀደም በአጠቃላይ  በኢትዮጵያ አለ ያለውን የፕሬስ ነጻነት ገደብም ሲያወግዝ ቆይቷል።


በሌላ በኩል የቃላት ውዝግብ ውስጥ ያሉት ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ወደ ሌላ ግጭት በመግባት ተጨማሪ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች እንዳይደርሱ  የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ስጋታቸውን እየገለጹ ነው።

 CPJ ትግራይ ክልልን ለጋዜጠኞች አደገኛ ስለማለቱ ፣ ስለኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት ይዞታ እናበኢትዮጵያ እና በኤርትራ አንዣቧል ስለተባለው የዳግም ግጭት ስጋት  የሰብዓዊ መብቶች ተከራካሪ እና የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ማዕከል ሃላፊ አቶ ያሬድ ኃይለማርያምን በስልክ አነጋግረናቸዋል።

DW Amharic

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...

በኦሮሚያ ክልል የ4.5 ሚሊዮን ዶላር የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ

ፈያ ኢንተግሬትድ ዴቬሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን በኦሮሚያ ክልል የሚከሰቱ የበሽታ ወረርሽኞችን...