የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንቱና ምክትላቸው ከሃላፊነታቸው ተሰናበቱ

Date:

የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንት ፀጋይ ብርሃነ ገ/ተኽለ እና ምክትላቸው ገብረኣምላኽ የዕብዮ ከስራ ገበታቸው ተሰናብተዋል።

በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ፊርማ ግንቦት 5/2017 ዓ.ም የተፃፈው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው ፥ ፕሬዜዳንቱና ምክትላቸው የስራ መልቀቅያ እንዲሰጣቸው  በጠየቁትና ባመለከቱት መሰረት ከምስጋና ጭምር ስንብት ተሰጥቶዋቸዋል።

በዚህም ፕሬዜዳንቱና ምክትላቸው ከዛሬ ግንቦት 6/2017 ዓ.ም ጀምሮ ከስራ መሰናበታቸው የተፃፈላቸው ደብዳቤ ያመለክታል።

ፕሬዜዳንቱ እና ምክትላቸው የቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ወደ ስልጣን መምጣታቸው ተከትሎ ወደ ሃላፊነት የመጡ ሲሆን ከአንዴም ሁለቴ ጊዜ ስራ ለመልቀቅ ጠይቀው ሳይሳካላቸው ቀርቷል።

የስራ መልቀቅያ እንዲያስገቡ እንደ ምክንያት ከጠቀሱዋቸው ችግሮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራ አስፈፃሚ አካላት በህግ ልዕልና የሚያሳዩት ያልተገባ ጣልቃ ገብነት መሆኑን ከዚህ ቀደም መግለጻቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃ ማድረጉ ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...