የደረሰኝ ህትመት ጠይቀው በሙሉ ወይም በከፊል ታትሞ ያልደረሳቸውና እና አስካሁን ለቅጽ/ቤት ያመለከቱ ግብር ከፋዮች የገቢዎች ሚኒስቴር በ5 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ እንዲያሳውቁ አሳስቧል።
ለከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት ግብር ከፋዮች በሙሉ በያሉበት በሚል በወጣው በዚህ ደብዳቤ ብርሀንና ሰላም ማተሚያ ቤት የቀረቡለትን የህትመት ትዕዛዞች በሙሉ አትሞ መጨረሱን ይገልጻል።
በዚህም፥ ከታህሳስ 1 ቀን 2017 እስክ ታህሳስ 30 ቀን 2018 የደረሰኝ ህትመት ጠይቃችሁ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ታትሞ ያልደረሳችሁ እና አስካሁን ለቅጽ/ቤቱ ያላመለከታችሁ ግብር ከፋዮች እንድታመለክቱም አስታውቋል።
