ሦስት አስርት ዓመታት በዘርፉ የቆየው ጊፍት ሪል ስቴት እስከአሁን ከ10 ቢሊየን ብር በላይ ሽያጭ ያከናወነ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀናት የቤት ኤክስፖ ማዘጋጀቱን ይፋ አድርጓል።
ጊፍት ሪል ስቴት የአፓርትመንትና የንግድ ሱቆችን ለሽያጭ ያቀረበው በ2 በመቶ ቅድመ ክፍያ እንደሆነም ነው ያስታወቀው።
በኤክስፖው እስከ 25 በመቶ ቅናሽ በማድረግ የቤት ባለቤት መሆን የሚያስችል ዕድልም ተመቻችቷል ነው የተባለው።
የሽያጭ ኤክስፖው ከመስከረም 29 እስከ ጥቅምት 8 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚካሄድ ሲሆን 1 ሺህ 500 ቤቶች ለሽያጭ ቀርበዋል።
በአራተኛውን የጊፍት ሜትሮፖሊታን መንደር፣ “የዋና ከተማችን ዋና ከተማ” በሆነው በለገሃር ላይ 4 ሺህ ቤቶችን በጥራት በመገንባት ላይ እገኛለሁ ብሏል።
ማህበራዊ ኃላፊነትን ከመወጣት አንፃርም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተረከበው መሬት ላይ በቦሌ ክፍለ ከተማ ለ30 አባወራ እንዲሁም በሰሚት ለ40 አቅም ለሌላቸው ዜጎች ቤት ማስረከቡን ገልጿል።
