ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

Date:

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ አቁም ማራዘማቸውን አስታወቁ። ትራምፕ የኢራን ወደቦች ላይ የተጣለው እገዳ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

ትራምፕ የተኩስ አቁሙን መራዘም ያስታወቁት ከመጠናቀቁ አንድ ቀን ቀደም ብሎ ነው።

የትራምፕ ውሳኔ ጦርነቱ ዳግም ይቀጥላል የሚለውን ፍራቻ ያስወገደ ሲሆን የሁለተኛው ዙር ድርድርም ቴህራን አቋሟን እስክታሳውቅ ድረስ ተራዝሟል።

ዶናልድ ትራምፕ የተኩስ አቁሙን ማራዘማቸውን ተከትሎ ምክትላቸው ጄዲ ቫንስ ወደ ኢዝላማባድ የሚያደርጉት ጉዞ መሰረዙን የዋይት ሐውስ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።

ኢራን ለትራምፕ ውሳኔ በይፋ መግለጫ ባትሰጥም ሁለቱም አገራት ያለ ስምምነት ጦረነቱን ለመቀጠል አንዳቸው ሌላኛቸው ላይ ሲዝቱ ነበር።

ትራምፕ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት መሠረት በፓኪስታን ጦር አዛዥ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ጥያቄ መሠረት እንዲሁም “የኢራን መንግሥት በከፍተኛ ሁኔታ በመፍረክረኩ” የተኩስ አቁሙ የኢራን መሪዎች እና ተወካዮች “የተቀናጀ ምክረ ሃሳብ ይዘው እስኪመጡ ድረስ” እንዲቀጥል መወሰናቸውን ተናግረዋል።

ትራም ፕበዚሁ መልዕክታቸው ላይ የአሜሪካ ባሕር ኃይል በኢራን ወደቦች ላይ “እገዳውን እንዲቀጥል” አዝዘዋል።የተኩስ አቁሙ ኢራን ምክረ ሃሳቧን እስክታቀርብ እና ውይይቶቹ የሚያመጡት ውጤት ምንም ይሁን ምን እስኪጠናቀቅ ድረስ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

ትራምፕ ከዚህ በፊት የተኩስ አቁሙን ለማራዘም ሃሳብ እንደሌላቸው ገልጸው ነበር። ምንም እንኳ ትራምፕ የኢራን ወደቦች ላይ የጣሉት እገዳ እንደሚቀጥል ቢናገሩም ከዚህ ቀደም የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ይህ “ከጦርነት ተግባር” አይተናነስም ሲሉ ኮንነውት ነበር።

በተባበሩት መንግሥታት የኢራን ልዑክ አሜሪካ በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የጣለችው እገዳ የምታነሳ ከሆነ ንግግሩ ይቀጥላል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።

BBC

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...