ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ  የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ገቡ

Date:

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቆይታቸው ከአገሪቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ እና በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ከዚህ ጉዟቸው ቀደም ብሎ ወደ ጅቡቲ በማቅናት የሶማሊያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ እና የጅቡቲ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ኢስማኢል ዑመር ጌሌ በተገኙበት የሦስትዮሽ ውይይት አካሂደዋል።

በውይይታቸው ላይ መሪዎቹ በሦስቱ አገራት መካከል ያለውን ዘርፈ ብዙ ትብብር ለማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።

ምክክር ከተገደረገባቸው ጉዳዮች አንዱ ሽብርተኝነትን በጋራ ለመዋጋትና በአፍሪካ ቀንድ አስተማማኝ ሰላም ማስፈን ነው።

የጋራ ኢንቨስትመንትን ማሳደግ፣ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትን ማጠናከር እና የቀጣናውን የኢኮኖሚ ውህደት ለማፋጠን የመሠረተ ልማት ትስስርን ስለማሳደግ ሰፊ ውይይት መደረጉን ከሶማሊያ ፕሬዜዳንት ፅ/ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...