ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስድስት ፖርቲዎች ከውድድር ውጪ ሆኑ

Date:



ለመጪው 7ኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ የዕጩዎች ምዝገባ አከናውነውና የምርጫ ምልክቶቻቸውን መርጠው ከነበሩት 48 የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ስድስቱ በተለያዩ ምክንያቶች ከፉክክሩ ውጪ መደረጋቸውን “ምርጫ 2018 – ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አረጋግጣለች።

ቦርዱ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን በውጭ አገር አሳትሞ ማጠናቀቁን ተከትሎ፣ ዘንድሮ የምርጫ ውድድሩ የሚካሄደው በተቀሩት 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ብቻ እንደሚሆን ታውቋል።

ከምርጫው ውድድር ውጪ ከሆኑት ፓርቲዎች መካከል ሦስቱ መሠረታቸውን በትግራይ ክልል ያደረጉ ሲሆኑ፣ እነርሱም በትግራይ ክልል ምርጫ ባለመካሄዱ ምክንያት ከውድድር የወጡት ዲሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት)፣ ትንሳኤ ሰብዓ እንደርታ እና ትንሳኤ ሥርዓት ቃንጪ ኃቂ ፓርቲዎች ናቸው።

የተቀሩት ሦስት ፓርቲዎች ደግሞ በአመራሮች የውስጥ ክፍፍልና በፍርድ ቤት ክርክር ሳቢያ ዕጩዎቹ የተሰረዙበት የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢሶዴፓ)፣ በበጀት ኦዲት ሪፖርት መዘግየት ምክንያት ምዝገባው ሳይሳካ የቀረው የሲዳማ ፌደራሊስት ፓርቲ (ሲፈፓ)፣ እንዲሁም ምክንያቱን በውል “አላውቀውም” ባለው ሁኔታ ከምርጫው የተሰረዘው እና ቦርዱን የሚወቅሰው የጋምቤላ ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ (ጋሕነን) መሆናቸው ታውቋል። [ምርጫ 2018 – ኢትዮጵያ ኢንሳይደር]

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...