ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

Date:

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ በ1.9 ቢሊዮን ብር የገነባውን ሆቴል በይፋ ሥራ ጀምሯል።

ሻለቃ ኃይሌ በምርቃቱ ላይ ባደረገው የምስጋና ንግግር፣ ደብረ ብርሃን የኢንዱስትሪ፣ የሥራ እና የጽናት ከተማ መሆኗን ጠቅሶ፤ ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ለአገልግሎት በመብቃቱ የተሰማውን ጥልቅ ደስታ ገልጿል።

አክሎም “እኛ ኢንቨስት ስናደርግ ትልቁ ዓላማችን የሥራ ዕድል መፍጠርና የአገራችንን ገጽታ መገንባት ነው” ብሏል።

ሆቴሉ ሲገነባ የነበሩ ፈተናዎችን በከተማዋ አስተዳደርና በሕዝቡ ድጋፍ ማለፍ እንደተቻለ የገለጸው ሻለቃ ኃይሌ፤ “ ‘አይቻልም’ የሚል ቃል በኢትዮጵያዊያን መዝገበ ቃላት ውስጥ መኖር የለበትም፤ በትጋትና በሥራ ካሰብንበት እንደርሳለን” ሲል የሥራን አስፈላጊነት አጽንኦት ሰጥቷል።

ይህ አዲስ የተመረቀው ሆቴል ለከተማዋ ተጨማሪ ውበትና የቱሪዝም መዳረሻ እንደሚሆን የተገለጸ ሲሆን፣ ማህበረሰቡም ይህን ታላቅ ሀብት እንዲንከባከበው ጥሪ ቀርቧል።

ሻለቃ ኃይሌ ለፕሮጀክቱ መሳካት ድጋፍ ላደረጉ አካላት በሙሉ ምስጋናውን አቅርቧል።

ይህ 11ኛው የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት ፕሮጀክት ለአካባቢው ነዋሪዎች ሰፊ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥርና ለከተማዋ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገልፁል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...