በቴሌኮም ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ማጭበርበሮችን የብሔራዊ መታወቂያን በመጠቀም ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ እንዳሉ ተገለፀ

Date:

በበርካታ ዘርፎች እንደ ቅድመ ሁኔታ እየተጠየቀ የሚገኘው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በቀጣይም በቴሌኮም ዘርፉ ላይ ማጭበርበሮችን ለመከላከል በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ተግባራዊ ለማድረግ ስራዎች መጀመራቸውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታውቋል።

በቅድመ ሁኔታ ተግባራዊ ሲደረግም የሲም ካርድ ቁጥጥር እና ያለአግባብ በሲም ካርዶች የሚፈፀሙ የብድር ማጭበርበሮችን ለማስቀረት እንደሚረዳ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የባለድርሻ አካላት ዳይሬክተር አቶ ሳሚናስ በላይነህ ተናግረዋል።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አንድ ማንነትን ለአንድ ግለሰብ የሚሰጥ በመሆኑ በአገልግሎት ሰጪ ማዕከላት ላይ የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እንደሚያግዝ እና ተቋማትን እንደሚያስተሳስርም ሃላፊው አንስተዋል።

እንዲሁም በትምህርት፣ በፋይናንስ እና በአገልግሎት መስጫ ተቋማት ላይ ተግባራዊ የሚደረገው ፋይዳ ነባር መታወቂያዎችን ተክቶ የሚያስቀር እንዳልሆነ አቶ ሳሚናስ ገልፀዋል ።

እስካሁን ባለውም በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ13 ሚሊየን በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ለማግኘት መመዝገባቸውን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...