በቴሌኮም ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ማጭበርበሮችን የብሔራዊ መታወቂያን በመጠቀም ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ እንዳሉ ተገለፀ

Date:

በበርካታ ዘርፎች እንደ ቅድመ ሁኔታ እየተጠየቀ የሚገኘው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በቀጣይም በቴሌኮም ዘርፉ ላይ ማጭበርበሮችን ለመከላከል በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ተግባራዊ ለማድረግ ስራዎች መጀመራቸውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታውቋል።

በቅድመ ሁኔታ ተግባራዊ ሲደረግም የሲም ካርድ ቁጥጥር እና ያለአግባብ በሲም ካርዶች የሚፈፀሙ የብድር ማጭበርበሮችን ለማስቀረት እንደሚረዳ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የባለድርሻ አካላት ዳይሬክተር አቶ ሳሚናስ በላይነህ ተናግረዋል።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አንድ ማንነትን ለአንድ ግለሰብ የሚሰጥ በመሆኑ በአገልግሎት ሰጪ ማዕከላት ላይ የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እንደሚያግዝ እና ተቋማትን እንደሚያስተሳስርም ሃላፊው አንስተዋል።

እንዲሁም በትምህርት፣ በፋይናንስ እና በአገልግሎት መስጫ ተቋማት ላይ ተግባራዊ የሚደረገው ፋይዳ ነባር መታወቂያዎችን ተክቶ የሚያስቀር እንዳልሆነ አቶ ሳሚናስ ገልፀዋል ።

እስካሁን ባለውም በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ13 ሚሊየን በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ለማግኘት መመዝገባቸውን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...