በቴሌኮም ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ማጭበርበሮችን የብሔራዊ መታወቂያን በመጠቀም ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ እንዳሉ ተገለፀ

Date:

በበርካታ ዘርፎች እንደ ቅድመ ሁኔታ እየተጠየቀ የሚገኘው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ በቀጣይም በቴሌኮም ዘርፉ ላይ ማጭበርበሮችን ለመከላከል በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ተግባራዊ ለማድረግ ስራዎች መጀመራቸውን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታውቋል።

በቅድመ ሁኔታ ተግባራዊ ሲደረግም የሲም ካርድ ቁጥጥር እና ያለአግባብ በሲም ካርዶች የሚፈፀሙ የብድር ማጭበርበሮችን ለማስቀረት እንደሚረዳ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የባለድርሻ አካላት ዳይሬክተር አቶ ሳሚናስ በላይነህ ተናግረዋል።

የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አንድ ማንነትን ለአንድ ግለሰብ የሚሰጥ በመሆኑ በአገልግሎት ሰጪ ማዕከላት ላይ የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እንደሚያግዝ እና ተቋማትን እንደሚያስተሳስርም ሃላፊው አንስተዋል።

እንዲሁም በትምህርት፣ በፋይናንስ እና በአገልግሎት መስጫ ተቋማት ላይ ተግባራዊ የሚደረገው ፋይዳ ነባር መታወቂያዎችን ተክቶ የሚያስቀር እንዳልሆነ አቶ ሳሚናስ ገልፀዋል ።

እስካሁን ባለውም በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ13 ሚሊየን በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን ለማግኘት መመዝገባቸውን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...

አዲስ አበባ፦ የዜጎች ቀይ መስመር!

(የግል አስተያየት) አዲስ አበባ የኢትዮጵያውያን መናገሻ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች ለዘመናት...

አብን የምክክሩን ውጤት ውድቅ አደረገ!

አብን በሀገራዊ ምክክሩ ማጠቃለያ ላይ የተፈጸመውን “ሕገ-ወጥ ጣልቃ-ገብነት” በመቃወም...