2ሺህ4መቶ93 ሄክታር መሬት ላይ የዛፍ አንበጣ መከሰቱን ሰምተናል።
ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት በትግራይ ክልል ግብርና ቢሮ ባለሙያ የሆኑት አቶ አበራ ሀጎስ፤ ከየካቲት 12 ጀምሮ በሰሜን ምዕራብ ዞን የዛፍ አንበጣ መከሰቱን ተናግረዋል፡፡
የዛፍ አንበጣው መነሻው በኤርትራ ድንበር እንደሆነ የገለፁት ባለሙያዉ፤ አሁን ላይ በዋናነት ያጠቃው ሰብሎችን፣ የእንስሳቱን የግጦሽ ሳር እና የዛፍ አይነቶችን እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
የአንበጣ ዝርያ ተንቀሳቃሽ እንዳልሆነና ከዚህ በፊትም ተከስቶ እንደነበረ ያነሱት አቶ አበራ፤ በአንድ ዛፍ ላይ ወይም በአንድ አካባቢ ብዙ ጊዜ የመቆየት እድል ስላለው የርብርብ ስራ መሠራት እንዳለበት አንስተዋል፡፡
1 ሺ ሁለት መቶ ሄክታር መሬት መከላከል መቻሉንም ነው የገለፁት።
የግብርና ሚኒስቴር አንድ መድኃኒት መርጫ መኪና መላኩን አንስተው ፤በቂ አይደለም የፌደራል መንግስት አስፈላጊዉን ተጨማሪ እርዳታ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።
Ethio fm 107.8
