በትግራይ  ከ2 ሺ ሄክታር በላይ መሬት በዛፍ አንበጣ ተወረረ

Date:

2ሺህ4መቶ93 ሄክታር መሬት ላይ የዛፍ አንበጣ መከሰቱን ሰምተናል።

ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት በትግራይ ክልል ግብርና ቢሮ ባለሙያ የሆኑት አቶ አበራ ሀጎስ፤ ከየካቲት 12 ጀምሮ በሰሜን ምዕራብ ዞን የዛፍ አንበጣ መከሰቱን ተናግረዋል፡፡

የዛፍ አንበጣው መነሻው በኤርትራ ድንበር እንደሆነ የገለፁት  ባለሙያዉ፤ አሁን ላይ በዋናነት ያጠቃው ሰብሎችን፣ የእንስሳቱን የግጦሽ ሳር እና የዛፍ አይነቶችን እንደሆነም ገልጸዋል፡፡

የአንበጣ ዝርያ ተንቀሳቃሽ እንዳልሆነና ከዚህ በፊትም ተከስቶ እንደነበረ ያነሱት አቶ አበራ፤ በአንድ ዛፍ ላይ ወይም በአንድ አካባቢ ብዙ ጊዜ የመቆየት እድል ስላለው የርብርብ ስራ መሠራት እንዳለበት አንስተዋል፡፡

1 ሺ ሁለት መቶ ሄክታር መሬት መከላከል መቻሉንም ነው የገለፁት።

የግብርና ሚኒስቴር አንድ መድኃኒት መርጫ መኪና መላኩን አንስተው ፤በቂ አይደለም የፌደራል መንግስት አስፈላጊዉን ተጨማሪ እርዳታ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።

Ethio fm 107.8

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...