በትግራይ  ከ2 ሺ ሄክታር በላይ መሬት በዛፍ አንበጣ ተወረረ

Date:

2ሺህ4መቶ93 ሄክታር መሬት ላይ የዛፍ አንበጣ መከሰቱን ሰምተናል።

ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት በትግራይ ክልል ግብርና ቢሮ ባለሙያ የሆኑት አቶ አበራ ሀጎስ፤ ከየካቲት 12 ጀምሮ በሰሜን ምዕራብ ዞን የዛፍ አንበጣ መከሰቱን ተናግረዋል፡፡

የዛፍ አንበጣው መነሻው በኤርትራ ድንበር እንደሆነ የገለፁት  ባለሙያዉ፤ አሁን ላይ በዋናነት ያጠቃው ሰብሎችን፣ የእንስሳቱን የግጦሽ ሳር እና የዛፍ አይነቶችን እንደሆነም ገልጸዋል፡፡

የአንበጣ ዝርያ ተንቀሳቃሽ እንዳልሆነና ከዚህ በፊትም ተከስቶ እንደነበረ ያነሱት አቶ አበራ፤ በአንድ ዛፍ ላይ ወይም በአንድ አካባቢ ብዙ ጊዜ የመቆየት እድል ስላለው የርብርብ ስራ መሠራት እንዳለበት አንስተዋል፡፡

1 ሺ ሁለት መቶ ሄክታር መሬት መከላከል መቻሉንም ነው የገለፁት።

የግብርና ሚኒስቴር አንድ መድኃኒት መርጫ መኪና መላኩን አንስተው ፤በቂ አይደለም የፌደራል መንግስት አስፈላጊዉን ተጨማሪ እርዳታ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።

Ethio fm 107.8

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...