በትግራይ  ከ2 ሺ ሄክታር በላይ መሬት በዛፍ አንበጣ ተወረረ

Date:

2ሺህ4መቶ93 ሄክታር መሬት ላይ የዛፍ አንበጣ መከሰቱን ሰምተናል።

ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት በትግራይ ክልል ግብርና ቢሮ ባለሙያ የሆኑት አቶ አበራ ሀጎስ፤ ከየካቲት 12 ጀምሮ በሰሜን ምዕራብ ዞን የዛፍ አንበጣ መከሰቱን ተናግረዋል፡፡

የዛፍ አንበጣው መነሻው በኤርትራ ድንበር እንደሆነ የገለፁት  ባለሙያዉ፤ አሁን ላይ በዋናነት ያጠቃው ሰብሎችን፣ የእንስሳቱን የግጦሽ ሳር እና የዛፍ አይነቶችን እንደሆነም ገልጸዋል፡፡

የአንበጣ ዝርያ ተንቀሳቃሽ እንዳልሆነና ከዚህ በፊትም ተከስቶ እንደነበረ ያነሱት አቶ አበራ፤ በአንድ ዛፍ ላይ ወይም በአንድ አካባቢ ብዙ ጊዜ የመቆየት እድል ስላለው የርብርብ ስራ መሠራት እንዳለበት አንስተዋል፡፡

1 ሺ ሁለት መቶ ሄክታር መሬት መከላከል መቻሉንም ነው የገለፁት።

የግብርና ሚኒስቴር አንድ መድኃኒት መርጫ መኪና መላኩን አንስተው ፤በቂ አይደለም የፌደራል መንግስት አስፈላጊዉን ተጨማሪ እርዳታ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።

Ethio fm 107.8

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...