በዶናልድ ትራምፕ በዓለ ሲመት ላይ የተገኙ አምስት ባለጸጎች ከ200 ቢሊዮን ዶላር በላይ ከስረዋል

Date:

የሪፐብሊካኑ ዕጩ ዶናልድ ትራምፕ ባሳለፍነው ሕዳር ወር ላይ የተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫን ማሸነፋቸው ይታወሳል።

ይህን ተከትሎ ጥር ወር ላይ ዶናልድ ትራምፕ 47ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሆነው ወዳጆቻቸው፣ የሀገራት መሪዎች እና ባለጸጎች በተገኙበት በይፋ በዓለ ሲመታቸው ተከብሯል።

በዚህ በዓል ላይ የተገኙ የዓለማችን ቀዳሚ ባለጸጎች በዝግጅቱ ላይ ከተገኙበት ቀን ጀምሮ ኪሳራ እያስመዘገቡ እንደሆነ ብሉምበርግ ዘግቧል።

እንደ ዘገባው ከሆነ የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳድር ዋነኛ አካል የሆኑት ኢለን መስክ ብቻ ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ ብቻ የ148 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ አስመዝግቧል።

እንዲሁም የአማዞን እና የዋሽንግተን ፖስት ጋዜጣ ባለቤቱ ጄፍ ቤዞስ 29 ቢሊዮን ዶላር እንደከሰረ ተገልጿል።

የአልፋቤቱ ሰርጌይ ብሪን 22 ቢሊዮን ዶላር፣ የሜታ ኩባንያ ባለቤቱ ማርክ ዙከርበርግ አምስት ቢሊዮን ዶላር እንዲሁም ፈረንሳዊው የፋሺን ኢንዱስትሪ ባለቤት በርናርድ አርናልት ደግሞ አምስት ቢሊዮን ዶላር መክሰራቸው በዘገባው ላይ ተጠቅሷል።

በአጠቃላይ 17 ኩባንያዎች ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ስልጣን ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ የ1 ነጥብ 4 ትሪሊዮን ዶላር ኪሳራ ደርሶባቸዋል ተብሏል።

ለባለጸጎቹ የገቢ መቀነስ ምክንያት ከተባሉት ውስጥ የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳድር አዳዲስ እርምጃዎች፣ ከሀገራት ጋር የገቡበት የንግድ እና ቀረጥ ውሳኔዎች እና የተወሰኑት ባለጸጎች ከአስተዳድሩ ጋር ጥብቅ ቁርኝት አድርገዋል መባሉ ዋነኞቹ እንደሆኑ ተገልጿል።

ቀዳሚ ጽሑፍ
ቀጣይ ጥሑፍ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...