ብርቅዬው የዋልያ አይቤክስ ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነሱ ምክንያት

Date:

ዓለም አቀፍ የተፈጥሮ ጥበቃ ሕብረት (IUCN) በቅርቡ ባደረገው ግምገማ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘው የዋልያ አይቤክስ ዝርያ ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ማሽቆልቆሉን ተከትሎ፤ «ለመጥፋት አደጋ በእጅጉ የተጋለጠ» በሚል መደቡ ውስጥ መካተቱን አስታወቀ።

የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ፖል ሾልት ሾልት እንደገለጹት የተደረጉ ተጨማሪ ጥናቶች በኢትዮጵያ ስሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ውስጥ ብቻ የሚገኘው ዋሊያ አይቤክስ ቁጥር አሁንም እያሽቆለቆለ መሆኑን ያሳያሉ።

በታህሳስ 2017 በተካሄደ ጥናት 271 ዋልያዎች ብቻ ተገኝተዋል ብለዋል። ይህም በአንድ ዓመት ውስጥ ከፍተኛ የቁጥር ማነስ መኖሩን አመላክቷል ብለዋል።

ለዝርያው መመናመን፤ ለሥጋና ለባህላዊ መድኃኒትነት የሚደረገው ሕገ-ወጥ አደን፣ የተፈጥሮ መኖሪያ መራቆት እና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው የሰዎች ድንበር መተላለፍ ቀዳሚ ምክንያቶች መሆናቸው በጥናት ተረጋግጧል ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጠቅላይ መሪ ለአባታቸው ግድያ “የበቀል እርምጃ” እንደሚወሰድ ተናገሩ

የኢራን ጠቅላይ መሪ ሞጅታባ ኻሜኒ በጽሑፍ ባስተላለፉት መልዕክት አባታቸው...

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የመጨረሻ ልምምዱን ሰርቷል

ቡድኑ ነገ የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ዙር የመልስ ጨዋታውን...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ለመደራደር አለመጠየቋን አስታወቀች

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ፤ አገራቸው...

ሱዳን ዉስጥ ለሦስት ዓመታት የተካሄደው ጦርነትን ሰለ ማቆም

የሱዳን ብሔራዊ ጦር ለሦስት ዓመታት የተካሔደውን ጦርነት ለማቆም አሜሪካ...