ትራምፕ የቲክቶክ የሽያጭ ስምምነት ከእግዱ በፊት እንደሚፈረም ገለጹ

Date:




ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቻይናው ባይት ዳንስ የቲክቶክን ድርሻ እንዲሸጥ ከኩባንያው ጋር የተጀመረው ድርድር መተግበሪያው ከፊታችን ቅዳሜ በኋላ በሀገረ አሜሪካ ከመታገዱ በፊት በስምምነት ፊርማ እንደሚጠናቀቅ አመላክተዋል።

ትራምፕ ቲክቶክ ቻይናዊ ያልሆነ ገዢ እንዲያፈላልግ እስከ ቅዳሜ ኤፕረል 5 ቀን ቀነ-ገደብ አስቀምጠዋል። ይህ ካልሆነ ግን ከብሔራዊ ደህንነት ጋር በተያያዘ መተግበሪያው በሀገረ አሜሪካ እገዳ እንደሚጣልበት አስጠንቅቀዋል።

ፕሬዚዳንቱ እሁድ ዕለት ጉዳዩን ለጋዜጠኞች ሲያብራሩ፥ “አቅሙ ያላቸው በርካታ ገዢዎች አሉን፣ ለቲክቶክ ከፍተኛ ፍላጎት አለ፤ ቲክቶክ በአሜሪካ ሕያው ሆኖ መቀጠሉን ማየት እፈልጋለሁ” ብለዋል።

170 ሚሊዮን አሜሪካውያን የሚጠቀሙበት የአጭር ቪዲዮ መተግበሪያ የቲክቶክ የድርሻ ሽያጭ ስምምነት እንዲሳካ ቻይና ለምትጫወተው ሚና እንደ ማበረታቻ የታሪፍ ቅናሽ ሊያደርጉላት እንደሚችሉም ተናግረዋል።

https://t.me/EBCNEWSNOW

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...