ትራምፕ የቲክቶክ የሽያጭ ስምምነት ከእግዱ በፊት እንደሚፈረም ገለጹ

Date:




ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቻይናው ባይት ዳንስ የቲክቶክን ድርሻ እንዲሸጥ ከኩባንያው ጋር የተጀመረው ድርድር መተግበሪያው ከፊታችን ቅዳሜ በኋላ በሀገረ አሜሪካ ከመታገዱ በፊት በስምምነት ፊርማ እንደሚጠናቀቅ አመላክተዋል።

ትራምፕ ቲክቶክ ቻይናዊ ያልሆነ ገዢ እንዲያፈላልግ እስከ ቅዳሜ ኤፕረል 5 ቀን ቀነ-ገደብ አስቀምጠዋል። ይህ ካልሆነ ግን ከብሔራዊ ደህንነት ጋር በተያያዘ መተግበሪያው በሀገረ አሜሪካ እገዳ እንደሚጣልበት አስጠንቅቀዋል።

ፕሬዚዳንቱ እሁድ ዕለት ጉዳዩን ለጋዜጠኞች ሲያብራሩ፥ “አቅሙ ያላቸው በርካታ ገዢዎች አሉን፣ ለቲክቶክ ከፍተኛ ፍላጎት አለ፤ ቲክቶክ በአሜሪካ ሕያው ሆኖ መቀጠሉን ማየት እፈልጋለሁ” ብለዋል።

170 ሚሊዮን አሜሪካውያን የሚጠቀሙበት የአጭር ቪዲዮ መተግበሪያ የቲክቶክ የድርሻ ሽያጭ ስምምነት እንዲሳካ ቻይና ለምትጫወተው ሚና እንደ ማበረታቻ የታሪፍ ቅናሽ ሊያደርጉላት እንደሚችሉም ተናግረዋል።

https://t.me/EBCNEWSNOW

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ይህንዓለም አቅናው የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆኑ

በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደጉ ከሚገኙ እና ከፍተኛ የባለአክስዮኖች ቁጥር ካላቸው...

ማዕቀቦች የኢራንን የኒውክሌር መርሃ-ግብር ቢያደናቅፉም መንግስቱን ሊጥሉ እንደማይችሉ ተገለጸ

ማዕቀቦች የኢራንን ወታደራዊ እና የኒውክሌር እንቅስቃሴዎች አስቸጋሪና ውድ እንዲሆኑ...

የአፍሪካ ሀገራት አዲስ የኢንቨስትመንት ፈንድ ይፋ አደረጉ

በአፍሪካ ሀገራት ላይ የተደቀነውን ከፍተኛ የብድር ጫና ለማቃለል እና...

ዶናልድ ትራምፕ “በቅርቡ” ሆርሙዝ የአሜሪካ ግዛት አካል እንደሚሆን ተናገሩ

ከኢራን ጋር ያለው ግጭት እየተባባሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የአሜሪካው...