ቻይና ለ 74 ሀገራት ከቪዛ ነፃ ጉዞን ፈቀደች

Date:

በዚህ ዝርዝር ዉስጥ አንድም የአፍሪካ አገር አልተካተተም፡፡

ከሐምሌ 16 ጀምሮ ተግባራዊ በሚደረገው በዚ የነፃ ቪዛ ጉዞ የተፈቀደላቸው 74 ሀገራት፤ ለ 30 ቀናት ወደ ቻይና ያለ ቪዛ መጓዝ እንደሚችሉ ተነግሯል።

የሀገሪቷን የቱሪዝም ገቢ ለማሳደግ ትግበራ ላይ ይውላል የተባለው ከቪዛ ነፃ ጉዞ፤ የአፍሪካ ሀገሮችን ግን ሳያካትት ቀርቷል ።

ይህ የነጻ ቪዛ ጉዞ በኮቪድ ምክንያት የተጎዳውን የሀገሪቷን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ በከፍተኛ ደረጃ እንዲያንሰራራ ይረዳል ተብሏል።

ሆኖም ቻይና ይህን ዕድል ለሌሎች አገራት ስትፈቅድ አንድም የአፍሪካ አገር ያለማካተቷ በአፍሪካ ያላትን ተሳትፎ ለማሳደግ በቅርብ ጊዜያት ካደረገችው ጥረት ጋር የሚቃረን ነው ሲል አፍሪካ ኒውስ ዘግቧል።

ሐምሌ 2 ቀን 2017 ዓ.ም

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ፑቲን እና ሺ ጂንፒንግ በቻይና ውይይት ያደርጋሉ 

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ወደ ቻይና የሚያደርጉትን መጪ ጉብኝት አስመልክቶ የክሬምሊን...

ከምዝገባ ካርድ ባሻገር፦ ለነገው ድምፅ የዛሬው ጥንቃቄ

ግዮን መጽሔት :- የምርጫ ካርድዎን በእጅዎ ይዘዋል? እንኳን ደስ...

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...