የአሜሪካው አማዞን 16,000 ሠራተኞችን እንደሚቀንስ ረቡዕ ማረጋገጡን ኒውስማክስ ዘገበ፡፡
ኩባንያው ካለፈው ጥቅምት ወር ጀምሮ የ30 ሺ ገደማ የሠራተኞች ቅነሳ ዕቅዱን ያጠናቀቀ ሲሆን፤ ከዚህ በኋላ ተጨማሪ ቅነሳ ስለመኖሩ የገለጸው ነገር የለም ተብሏል፡፡
1.58 ሚሊዮን ሰራተኞች ላሉት አማዞን፣ የ30 ሺ ሠራተኞች ቅነሳ ከጠቅላላ የሰው ሃይሉ 10 በመቶውን የሚወክል ነው፡፡
ባለፈው ጥቅምት ወር ኩባንያው 14 ሺ ሠራተኞችን የቀነሰ ሲሆን፤ ለቅነሳው ሰበብ አድርጎ ያቀረበው ሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የኩባንያ የአሰራር ባህል መለወጥን እንደነበር ዘገባው አስታውሷል፡፡
