አማዞን በ3 ወራት 30ሺ ሠራተኞችን መቀነሱ ተነገረ

Date:

የአሜሪካው አማዞን 16,000 ሠራተኞችን እንደሚቀንስ ረቡዕ ማረጋገጡን ኒውስማክስ ዘገበ፡፡

ኩባንያው ካለፈው ጥቅምት ወር ጀምሮ የ30 ሺ ገደማ የሠራተኞች ቅነሳ ዕቅዱን ያጠናቀቀ ሲሆን፤ ከዚህ በኋላ ተጨማሪ ቅነሳ ስለመኖሩ የገለጸው ነገር የለም ተብሏል፡፡

1.58 ሚሊዮን ሰራተኞች ላሉት አማዞን፣ የ30 ሺ ሠራተኞች ቅነሳ ከጠቅላላ የሰው ሃይሉ 10 በመቶውን የሚወክል ነው፡፡

ባለፈው ጥቅምት ወር ኩባንያው 14 ሺ ሠራተኞችን የቀነሰ ሲሆን፤ ለቅነሳው ሰበብ አድርጎ ያቀረበው ሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የኩባንያ የአሰራር ባህል መለወጥን እንደነበር ዘገባው አስታውሷል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...