አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአጭር ጊዜ የሙያ ስልጠናዎችን መስጠት ሊጀምር ነው

Date:

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ የአጭር ጊዜ የሙያ ስልጠናዎችን መስጠት እንደሚጀምር አስታወቀ፡፡

ዩኒቨርሲቲው ሴኔት የአጭር ጊዜ የፕሮፌሽናል ሰርቲፊኬት መርኃ ግብሮችን ለመተግበር የሚያስችል ማዕቀፍ ማፅደቁን የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ለኢቢሲ ዶትስትሪም ገልጸዋል፡፡

ሴኔቱ ያፀደቀው የአጭር ጊዜ የፕሮፌሽናል ሰርቲፊኬት መርኃ ግብር የሰራተኞችን ዕውቀትና ክህሎት ለማሳደግ የሚረዳ መሆኑንም ፕሬዝዳንቱ ጠቅሰዋል፡፡

ማዕቀፉ በሚታወቅ ደረጃ ተምረው የተመረቁ ሙያተኞች በስራ ላይ ሆነው የሙያ  ክህሎታቸውን ለማስፋት እና ለማሳደግ ከሳምንታት እስከ ወራት የሚሰጥ ሙያዊ ስልጠና ነው ብለዋል፡፡

እንደዚህ አይነት የአጭር ጊዜ የፕሮፌሽናል ስልጠናዎች በፍጥነት ለሚለዋወጠው ገበያ ምላሽ ለመስጠት የሚረዳ እና ሙያተኞች የእድሜ ልክ ተማሪ የሚሆኑበትን ትልቅ ዕድል የሚፈጥር ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡

ስልጠናው የሚሰጠው በተለመደው የትምህርት ስርዓት አሰጣጥ ሳይሆን ኢንዱስትሪዎች፣ የሙያ ማህበራት ወይንም ሴክተር መስሪያ ቤቶች በሚያስፈልጋቸው ጉዳይ ላይ በጀማሪ፣ በመካከለኛ እና በከፍተኛ ደረጃ ለሙያተኞቻቸው የሚሆን የሙያ ሰርተፍኬት ሲፈልጉ የሚሰጥ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አብራርተዋል፡፡

እንደዚህ አይነት ስልጠናዎች ሰራተኞች የሚያጋጥማቸውን የዕውቀትና የክህሎት ክፍተት  ለመሙላት እና ለማሳደግ የሚረዳ ሲሆን እንደ የደረጃው ከሳምንታት እስከ ወራት የሚሰጥ ይሆናልም ብለዋል፡፡

ማዕቀፉ በተደራጀ ቅርፅ ለባለሙያዎች፣ ለኢንዱስትሪዎች እና ለሙያ ማህበራት ፍላጎቶች ምላሽ የሚሰጡ ችግር ፈቺ የሥልጠና ፕሮግራሞችን ለመስጠት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑንም ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...