የአሜሪካ የመከላከያ ሚኒስትር ፔት ሄግሴት እና የጦር ኃይሎች የጋራ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ዳን ኬይን በኢራን ላይ እየተካሄደ ስላለው ወታደራዊ ዘመቻ ቨርጂኒያ ከሚገኘው የፔንታጎን ዋና ጽህፈት ቤት መግለጫ ሰጥተዋል።
- የመከላከያ ሚኒስትሩ የአሜሪካ ጦር ኃይል በሕንድ ውቅያኖስ ላይ አንድ “የኢራን የጦር መርከብ” በውሃ ውስጥ የሚምዘገዘግ ሚሳዔል በመጠቀም ማስመጡን ተናግረዋል።
- የኢራን መንግሥት “ተሸንፏል” ያሉት የመከላከያ ሚኒስትሩ፤ አሜሪካ “በማያጠራጥር ሁኔታ፣ ያለርህራሄ፣ ከባድ ጉዳት በማድረስ እያሸነፈች ነው” ብለዋል።
- ተጨማሪ ወታደራዊ እርምጃ በኢራን ላይ እንደሚወሰድ ጠቅሰው፤ “የበለጠ እና ግዙፍ የጥቃት ማዕበል እየመጣ ነው” ብለዋል።
- የአሜሪካ ጦር ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ዳን ኬን በበኩላቸው የሠራዊቱ ጥቃት “ወደ ምድር እየተስፋፋ ወደ ኢራን ግዛት ጠልቆ እየገባ ነው” ሲሉ ጥቃቱ መጠናከሩን አመልክተዋል።
- የመከላከያ ሚኒስትሩ ፒት ሄግሴት ኢራን ፕሬዝዳንት ትራምፕን “ለመግደል” ሞክራለች በማለት ከስሰው፤ ነገር ግን አሜሪካ “ለመግደል ሙከራውን ያደረገውን ቡድን መሪ አድና ገድላለች” ብለዋል።
- ኢራን ውስጥ 150 በላይ ሰዎች የተገደሉበት በሴቶች ትምህርት ቤት ላይ ስለተፈጸመው ጥቃት ተጠይቀው የመከላከያ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ “ምርመራ” እያደረገች ነው ሲሉ መልሰዋል። ነገር ግን ጥቃቱ በእስራኤል ወይስ በአሜሪካ መፈጸሙን እንዲያረጋግጡ ቢጠየቁም ፈቃደኛ አልሆኑም።
