ኢትዮጵያና ሩዋንዳ የመከላከያ ትብብራቸውን ለማዘመን ተስማሙ

Date:

ኢትዮጵያ እና ሩዋንዳ ያላቸውን ታሪካዊ የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ በማጠናከር፣ የመከላከያ ዘርፉን በዘመናዊ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) ቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ መግባባት ላይ ደርሰዋል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ከሩዋንዳ መከላከያ ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄኔራል ሮናልድ ሪቪዋንጋ ጋር በነበራቸው ውይይት፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የቆየ ወታደራዊ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር መክረዋል።

በውይይቱ ወቅት ሁለቱም ወገኖች ወቅታዊ የደህንነት ተግዳሮቶችን ለመቋቋም ወታደራዊ ተግባራትን በቴክኖሎጂ ማዘመን ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። በተለይም ወታደራዊ ስምሪቶችን በፈጣንና በዘመናዊ መንገድ መምራት፤ የደህንነት ስጋቶችን ቀድሞ ለመተንበይና ለመተንተን የሰው ሠራሽ አስተውሎትን መጠቀም፤ የላቁ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የሀገራቱን የመከላከል አቅም ማጎልበት በሚሉ ነጥቦች ላይ የጋራ መግባባት ተፈጥሯል።

ይህ አዲስ የትብብር አቅጣጫ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ወታደራዊ ዲፕሎማሲ ከማጠናከሩ ባለፈ፣ ለአፍሪካ ቀንድና ለምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ሰላምና ደህንነት ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ታምኖበታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...