“ኢትዮጵያ የባሕር በር አያስፈልጋትም የሚል የፖለቲካ ፓርቲ ካለ መሰረዝ ነው ያለበት”

Date:


ኢትዮጵያ የባሕር በር አያስፈልጋትም የሚል የፖለቲካ ፓርቲ ካለ ከፓርቲነት ተሰርዞ ከፖለቲካው ምዕራፍ መውጣት እንዳለበት የኢዜማ አመራርና የአዲስ አበባ ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ግርማ ሰይፉ ተናገሩ።

አቶ ግርማ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ የሀገሪቱን የባሕር በር የማረጋገጥ ጉዳይ በቀጣይ ሕገ-መንግሥቱ በሚሻሻልበት ወቅት ትኩረት ተሰጥቶት የመንግሥት ግዴታ ተደርጎ ሊደነገግ ይገባል።

ለዚህም እንደ ምሳሌ ያነሱት የግብፅ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 19 የናይልን ውኃ ደኅንነት ማስጠበቅ የመንግሥት ግዴታ መሆኑን እንደሚደነግግ ጠቅሰው፣ በኢትዮጵያም የባሕር በርን ማስጠበቅ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታ ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።


ብሔራዊ ጥቅምን የማስከበር ኃላፊነት በመንግሥት ላይ መጣል እንዳለበት የገለጹት አቶ ግርማ፤ ከዚህ ብሔራዊ ጥቅም በተቃራኒ የሚቆሙ አካላትን መቆጣጠር የመንግሥት ግዴታ ሊሆን እንደሚገባም አመልክተዋል።

የባሕር በር ጥያቄ ከፖለቲካ ወገንተኝነት ባለፈ የሀገር ህልውና ጉዳይ መሆኑንና ማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት ለዚህ ግብ መሳካት ቅድሚያ መስጠት እንዳለበትም በአጽንኦት ገልጸዋል።

ጋዜጣ_ፕላስ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...