ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በቻይና የሁዋዌ ውድድርን አንደኛ በመሆን አሸነፉ

Date:

የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ቡድን የሁዋዌ “ቴክ ፎር ጉድ ግሎባል – Tech4Good” ውድድርን አንደኛ በመሆን አሸንፈዋል። ከቡድኑ አባላት መካከል አንዱ የሆነው አብዲ ገረመው ሲሆን፤ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር #INSA በ2016 ዓ.ም ባካሄደው የሳይበር ታለንት ሰመር ካምፕ ፕሮግራም ከተሳተፉና ከተመረቁ ባለ ልዩ ተሰጥኦ ወጣቶች መካከል አንዱ ነው፡፡ አብዲ ገረመው ከውድድሩ በኋላ ባስተላለፈው መልዕክት በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የሳይበር ልሕቀት ማዕከል ያሳለፈው ጊዜ ውድድሩን ለማሸነፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳበረከተለት ገልጿል፡፡

ውድድሩ በቻይና ቤጂንግ እና ሼንዘን የሚገኙ የቴክኖሎጂ ማዕከሎችን ጉብኝትና የተግባር ስልጠናዎችን ካካተተው ዝግጅት ጋር የተካሄደ ነው።

በስድስት ተማሪዎች የተወከለው የኢትዮጵያ ቡድን ተማሪዎቹን ያሰባሰበው፤ ከአዲስ አበባ፣ ከሐረማያ፣ ከጅማ፣ ከወልቂጤ እና ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ (AASTU) ዩኒቨርስቲዎች ነው።

ቡድኑ በውድድሩ ከሞሮኮ፣ ደቡብ አፍሪካ፤ አርጀንቲና፣ አየርላንድ፣ ማላዊ፣ ቬትናም፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስና ሌሎችን ጨምሮ ከዓለም ዙሪያ ከተውጣጡ 12 ልዩ ቡድኖች ጋር ተወዳድሯል።

የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ቡድን አሸናፊ የሆነው የእንስሳትን ህመሞች አስቀድሞ ለመለየት በተዘጋጀውና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) በጎለበተው ኧርሊ ቬት (EarlyVet) በተሰኘው ፕሮጀክታቸው ነው፡፡

ይህ የፈጠራ ፕሮጀክት ከተባበሩት መንግስታት የዘላቂ ልማት ግቦች (SDGs) በተለይም ግብ 2 ” ዜሮ ርሃብ ” እና ግብ 15 ” ህይወት በምድር ” ከሚለው ጋር የተጣጣመ መሆኑና በግብርና እና በእንስሳት ጤና ላይ ያሉ ወሳኝ ተግዳሮቶችን ይፈታል ተብሎ እንደሚታመን በውድድሩ ተብራርቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...