ኢትዮጵያ የህዝብ ትራንስፖርት ዘርፍ ተምሳሌታዊ ለውጥ በማስመዝገብ ላደረገችው ልዩ ጥረት ዛሬ በኢስዋቲኒ ታላቅ ሽልማት አግኝታለች።
ሽልማቱን የሰጡት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ የመንገድ ደህንነት ልዩ መልዕክተኛ ሚስተር ዣን ቶድት ከኢስዋቲኒ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር በመሆን ነው።
ይህ ሽልማት ኢትዮጵያ ዘላቂ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ቀልጣፋ የህዝብ ማመላለሻ ስርዓቶችን ለማራመድ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል።
እውቅናው በአህጉሪቱ የመንገድ ደህንነት እና የትራንስፖርት ትራንስፎርሜሽን መለኪያዎችን በማስቀመጥ ሀገሪቱ እያደገች ያለችውን ሚና ያሳያል።
በስነስርዓቱ ላይ ኢትዮጵያን ወክለው እየተሳተፋ ሚገኙት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር በረኦ ሀሰን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት “በዚህ ስኬት በእውነት ኩራት ይሰማናል፣ በመንገድ ደህንነት ላይ ያለንን ሁለንተናዊ ትኩረት እንድንጠብቅና በዘርፋ ግስጋሴያችንን እንድንቀጥል ያበረታታናል ብለዋል።
