ኢትዮጵያ በህዝብ ትራንስፖርት ዘርፍ ተምሳሌታዊ ለውጥ በማስመዝገብ ተሸለመች

Date:

ኢትዮጵያ የህዝብ ትራንስፖርት ዘርፍ ተምሳሌታዊ ለውጥ በማስመዝገብ ላደረገችው ልዩ ጥረት ዛሬ በኢስዋቲኒ ታላቅ ሽልማት አግኝታለች።

ሽልማቱን የሰጡት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ የመንገድ ደህንነት ልዩ መልዕክተኛ ሚስተር ዣን ቶድት ከኢስዋቲኒ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር በመሆን ነው።

ይህ ሽልማት ኢትዮጵያ ዘላቂ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ቀልጣፋ የህዝብ ማመላለሻ ስርዓቶችን ለማራመድ ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል።

እውቅናው በአህጉሪቱ የመንገድ ደህንነት እና የትራንስፖርት ትራንስፎርሜሽን መለኪያዎችን በማስቀመጥ ሀገሪቱ እያደገች ያለችውን ሚና ያሳያል።

በስነስርዓቱ ላይ ኢትዮጵያን ወክለው እየተሳተፋ ሚገኙት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር በረኦ ሀሰን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት “በዚህ ስኬት በእውነት ኩራት ይሰማናል፣ በመንገድ ደህንነት ላይ ያለንን ሁለንተናዊ ትኩረት እንድንጠብቅና በዘርፋ ግስጋሴያችንን እንድንቀጥል ያበረታታናል ብለዋል።

https://www.facebook.com/share/p/1EAxTN8E3f

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...